ኬኒያ ለአዳዲስ የንግድ ባንኮች በሯን ልትከፍት ነው
13:43 17.04.2025 (የተሻሻለ: 14:04 17.04.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ኬኒያ ለአዳዲስ የንግድ ባንኮች በሯን ልትከፍት ነው
የኬኒያ ማዕከላዊ ባንክ ከአሥር ዓመታት በላይ በአዲስ የንግድ ባንኮች ፈቃድ ላይ የጣለውን እገዳ ከፈረንጆቹ ሰኔ 1 ጀምሮ እንደሚያነሳ አስታውቋል።
እ.አ.አ ከ2015 ጀምሮ የተጣለው እገዳ በባንክ ዘርፉ ሕጋዊ እና የቁጥጥር ማዕቀፍ ላይ ከታየው ከፍተኛ መሻሻል በኋላ እንደሚነሳ ተገልጿል።
የኬኒያ ማዕከላዊ ባንክ በቅርቡ የአነስተኛ ካፒታል መጠን በአሥር እጥፍ ጨምሮ 10 ቢሊዮን የኬኒያ ሽልንግ (77 ሚሊዮን ዶላር) መድረሱ የንግድ ባንክ ዘርፉን የበለጠ አስተማማኝ አድርጎታል ብሏል።
@sputnik_ethiopia