የኢትዮጵያ መምህራን የኅብረት ሥራ ባንክ በቀጣይ ዓመት ሥራ ሊጀመር ይችላል ተባለ
18:20 16.04.2025 (የተሻሻለ: 18:44 16.04.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
የኢትዮጵያ መምህራን የኅብረት ሥራ ባንክ በቀጣይ ዓመት ሥራ ሊጀመር ይችላል ተባለ
ባንኩ በመምህራን ላይ እየጨመረ ያለውን የገንዘብ ጫና ለማቃለል እና ተመጣጣኝ የብድር እና የቤት ድጋፍ ለመስጠት ያለመ ልዩ የፋይናንስ ተቋም መሆኑን የትምህርት ሚኒስትር ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ለፓርላማ አባላት ተናግረዋል።
"የመምህራን የኅብረት ሥራ ባንኩ የአስተማሪዎቻችንን ኑሮ ለማሻሻል ትልቅ እርምጃ ይሆናል፡፡ የባንኩ መጀመር መምህራን የራሳቸውን ቤት ለመገንባት የሚያስችል መሬት መመደቡ ላይ የተመሠረተ ነው” ብለዋል።
መንግሥት አስፈላጊውን ድጋፍ ካደረገ ባንኩ በሚቀጥለው ዓመት መጀመሪያ ሥራ ሊጀምር እንደሚችል ጠቁመዋል።
@sputnik_ethiopia