ኢትዮጵያ የሱዳን ግጭት አፈታት በሱዳናውያን ሊመራ ይገባል አለች
11:10 16.04.2025 (የተሻሻለ: 11:34 16.04.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ኢትዮጵያ የሱዳን ግጭት አፈታት በሱዳናውያን ሊመራ ይገባል አለች
ኢትዮጵያ በእንግሊዝ ለንደን በተካሄደው የሱዳን ጉባኤ ላይ ተሳትፋለች፡፡ በእርዳታ አቅርቦት፣ የተኩስ አቁም እና ለግጭቱ ፖለቲካዊ መፍትሄ ማምጣት ትኩረቱን ባደረገው ስብሰባ ላይ በብሔራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን የተመራ ልዑክ ተሳትፏል፡፡
አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን የሱዳን ጦርነትን ለማስቆም የተሟላ እና አሳታፊ መፍትሔ እንደሚያሻ ተናግረዋል፡፡ ንፁሃንን ለመጠበቅ እና ያለማንም እንቅፋት የሰብዓዊ እርዳታ አቅርቦት እንዲገባ ዘላቂ የሆነ የተኩስ አቁም ስምምነት ላይ መድረስ አስቸኳይ ጉዳይ ነውም ብለዋል።
በተጨማሪም ዓለም አቀፉ ማሕበረሰብ ለሱዳን እና ስደተኞን ለሚያስጠልሉ ጎረቤት ሀገራት የሚያደርገውን ድጋፍ እንዲጨምር ጠይቀዋል ሲል ያስታወቀው የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ነው፡፡
© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱ

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱ
