የኮሎምቢያ ምክትል ፕሬዝዳንት የአፍሪካ የዘር ሀረግ ያላቸውን ሰዎች ሰብዓዊ ክብር በማካካሻ ፍትሕ መመለስ አስፈላጊ እንደሆነ ተናገሩ
11:07 15.04.2025 (የተሻሻለ: 11:44 15.04.2025)
© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱየኮሎምቢያ ምክትል ፕሬዝዳንት የአፍሪካ የዘር ሀረግ ያላቸውን ሰዎች ሰብዓዊ ክብር በማካካሻ ፍትሕ መመለስ አስፈላጊ እንደሆነ ተናገሩ

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
የኮሎምቢያ ምክትል ፕሬዝዳንት የአፍሪካ የዘር ሀረግ ያላቸውን ሰዎች ሰብዓዊ ክብር በማካካሻ ፍትሕ መመለስ አስፈላጊ እንደሆነ ተናገሩ
ፍራንሲያ ማርኬዝ ሰኞ እለት በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት በተካሄደውና ዘርዓ አፍሪካውያንን ትኩረቱ ባደረገው ፎረም ላይ ባደረጉት ንግግር ቅኝ ገዢ ኃይሎች ለዘመናት ለዘለቀው የባርነት አገዛዝ እና አሁንም ድረስ ለቀጠለው ተፅዕኖው ኃላፊነት እንዲወስዱ ጠይቀዋል።
"የዚያ ሥርዓት ጉዳት እና ውጤት አሁንም እየደረሰብን ነው" በማለት በመኖሪያ ቤት፣ በጤና እና በትምህርት ዘርፎች የቀጠሉትን አለመመጣጠኖች ጠቁመዋል ሲሉ መገናኛ ብዙሃን ዘግበዋል፡፡
ውይይቱ በሰው ሰራሽ አስተውሎት የዘር መድልዎ እየተንጸባረቀ እንደሆነም ዳሷል። የተባበሩት መንግሥታት ኃላፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ አዳዲስ ቴክኖሎጂዎችን "ከአድልዎ ነጻ" ለማድረግ እርምጃ እንዲወሰድ ጥሪ አቅርበዋል።