ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ቬይትናም ውስጥ የፀሐይ ፓነሎችን የሚያመርተው ቶዮ ሶላር በኢትዮጵያ የሚያደርገውን እንቅስቃሴ እንዲያሰፋ ጠየቁ
10:46 15.04.2025 (የተሻሻለ: 11:14 15.04.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ቬይትናም ውስጥ የፀሐይ ፓነሎችን የሚያመርተው ቶዮ ሶላር በኢትዮጵያ የሚያደርገውን እንቅስቃሴ እንዲያሰፋ ጠየቁ
ጠቅላይ ሚኒስትሩ እና ቀዳማዊት እመቤት ዝናሽ ታያቸው ከቬትናም ኤክስፖርት የሚያደርገውን የጃፓን ኩባንያ ቶዮ ሶላር የሥራ እንቅስቃሴን ጎብኝተዋል፡፡
ኩባንያው በቅርቡ በሐዋሳ ኢንዱስትሪ ፓርክ አዲስ ፋብሪካውን በመክፈት በኢትዮጵያ ውስጥ ሥራ የጀመረ ሲሆን ድርጀቱ የፀሃይ ፓነሎችን ከማምረት ባለፈ ኢትዮጵያ ውስጥ የኃይል ጣቢያ ማቋቋምን ጨምሮ በተለያዩ ዘርፎች እንዲሳተፍ አብረታትዋል፡፡ ይህም እያደገ የመጣውን የኢትዮጵያን የኃይል ፍላጎት ለሟሟላት ከሚደረገው ጥረት ጋር የሚጣጣም እንደሆነ የጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት አስታውቋል፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ እና ቀዳማዊ እመቤት ዝናሽ ታያቸው በቬትናም ሃኖይ ይፋዊ የሥራ ጉብኝት እያደረጉ ነው። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በ2025ቱ የP4G ቬትናም ጉባኤ ላይ ይሳተፋሉ ተብሎም ይጠበቃል።