ዊሊያም ሩቶ የምግብ ዋስትና ችግርን ለመቅረፍ የሀገሪቱ ግብርና ዘርፍ ማሻሻያ ያሻዋል አሉ
20:12 14.04.2025 (የተሻሻለ: 20:44 14.04.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ዊሊያም ሩቶ የምግብ ዋስትና ችግርን ለመቅረፍ የሀገሪቱ ግብርና ዘርፍ ማሻሻያ ያሻዋል አሉ
ማሻሻያው የበቆሎ ምርት እጥረትን መቅረፍ፣ የአርሶ አደሮችን ገቢ ማሳደግ እና ኬኒያ ከውጭ በሚገቡ ምርቶች ላይ ያላትን ጥገኛነት መቀነስ ላይ ያነጣጠረ እንደሆነ ፕሬዝዳንቱ ተናግረዋል።
የኬኒያው ፕሬዝዳንት የግብርና ካቢኔ ሴክሬታሪው ሙታሂ ካግዌ የዘመናዊ ቴክኖሎጂዎች ትግበራን እንዲያፋጥኑ ኃላፊነት ተሰጥቷቸዋል።
ፕሬዝዳንቱ ይፋ ያደረጓቸው ቁልፍ እርምጃዎች፦
⏺ በግብርና አቅርቦት ውስጥ በሕገ-ወጥ ደላሎች የተፈጠረውን ሰንሰለት ማፈራረስ።
⏺ ውጤማ ያልሆኑ የእርሻ ልምዶችን እና የግብዓት እጥረቶችን መፍታት።
⏺ በቡና፣ ወተት እና ስኳር ዘርፍ ላይ በግብዓት ድጎማ፣ በተሻለ ዋጋ እና በተረጋገጠ ገበያ ማሻሻያ ማድረግ።
ከግብርና ባሻገር ከአፍሪካ ልማት ባንክ በሚገኝ 4.6 ሚሊዮን ዶላር የኤሌክትሪክ ኃይል ፕሮጀክት ለማስጀመር ማቀዳቸውንም ፕሬዝዳንት ሩቶ አስታውቀዋል።