ኢትዮጵያ ቤላሩስ በባለብዙ ወገን መድረኮች ላይ ለምታደርገው ድጋፍና ለምታሳየው ገለልተኛ አቋም ምስጋና አቀረበች
17:20 14.04.2025 (የተሻሻለ: 17:34 14.04.2025)
© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱኢትዮጵያ ቤላሩስ በባለብዙ ወገን መድረኮች ላይ ለምታደርገው ድጋፍና ለምታሳየው ገለልተኛ አቋም ምስጋና አቀረበች

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ኢትዮጵያ ቤላሩስ በባለብዙ ወገን መድረኮች ላይ ለምታደርገው ድጋፍና ለምታሳየው ገለልተኛ አቋም ምስጋና አቀረበች
የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር በለጠ ሞላ ከቤላሩስ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማክሲም ራይዠንኮቭ ጋር በዛሬው እለት ውይይት አክሂደዋል፡፡
ውይይቱ በተለያዩ ዘርፎች ላይ በጋራ በመሥራት የኢትዮጵያና የቤላሩስን የሁለትዮሽ ግንኙነት ይበልጥ ማጠናከር ላይ ትኩረቱን ያደረገ እንደነበር የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር አስታውቋል።
ሚኒስትር በለጠ ሞላ ሚንስክ በባለብዙ ወገን መድረኮች ለኢትዮጵያ የምታደርገውን ድጋፍ አጠናክራ እንድትቀጥልም ጠይቀዋል።
የቤላሩስ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሀገራቸው በቴክኖሎጂ፣ በግብርና፣ በትምህርት፣ በማዕድን፣ በንግድ፣ በኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂና በሌሎች ዘርፎች ዙሪያ ከኢትዮጵያ ጋር በትብብር ለመሥራት ዝግጁ መሆኗን ገልጸዋል፡፡
© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱ

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱ
