የጋቦኑ የሽግግር ጊዜ ፕሬዝዳንት ብራይስ ኦሊጊዊ ንግዌማ በሀገሪቱ የተካሄደውን ምርጫ አሸነፉ
13:21 14.04.2025 (የተሻሻለ: 13:44 14.04.2025)
© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱየጋቦኑ የሽግግር ጊዜ ፕሬዝዳንት ብራይስ ኦሊጊዊ ንግዌማ በሀገሪቱ የተካሄደውን ምርጫ አሸነፉ

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
የጋቦኑ የሽግግር ጊዜ ፕሬዝዳንት ብራይስ ኦሊጊዊ ንግዌማ በሀገሪቱ የተካሄደውን ምርጫ አሸነፉ
የሀገር ውስጥ እና የደህንነት ሚኒስትር ሄርማን ኢሞንጋልት ንጉዌማ 90.35 በመቶ ድምጽ ማግኘታቸውን አስታውቀዋል።
የንግዌማ ዋና ተቀናቃኝ የነበሩት የቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር አሌን ክሎድ ቢሊ ባይ ንዜ 3.02 በመቶ ድምጽ በማግኘት ሁለተኛ ደረጃን አግኝተዋል።
በአጠቃላይ በምርጫው ከ920 ሺህ በላይ መራጮች የተመዘገቡ ሲሆን ከእነዚህ ውስጥ ከ28 ሺህ በላይ የሚሆኑት ከሀገር ውጭ የተመዘገቡ ናቸው ተብሏል፡፡
እንደ ኢሞንግልት ገለፃ የመራጮች ተሳትፎ 70.4 በመቶ ነበር።