የቤላሩስ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማክሲም ሪዜንኮቭ የኢትዮጵያ የንግድ ማሕበረሰብ በቤላሩስ የንግድ ትርዒቶች ላይ እንዲሳተፍ ግብዣ አቀረቡ
11:19 14.04.2025 (የተሻሻለ: 11:34 14.04.2025)
© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱየቤላሩስ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማክሲም ሪዜንኮቭ የኢትዮጵያ የንግድ ማሕበረሰብ በቤላሩስ የንግድ ትርዒቶች ላይ እንዲሳተፍ ግብዣ አቀረቡ

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
የቤላሩስ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማክሲም ሪዜንኮቭ የኢትዮጵያ የንግድ ማሕበረሰብ በቤላሩስ የንግድ ትርዒቶች ላይ እንዲሳተፍ ግብዣ አቀረቡ
ለይፋዊ የሥራ ጉብኝት አዲስ አበባ የሚገኙት የቤላሩስ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ከኢትዮጵያ አቻቸው ጋር መክረዋል።
የኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቴዎስ የኢትዮጵያ እና ቤላሩስ የንግድ እና ኢኮኖሚ ትብብር ኮሚሽን ለሀገራቱ የሁለትዮሽ የንግድ ልውውጥ ዋና መሳሪያ መሆን አለበት የሚለውን የቤላሩስን አቋም ደግፈዋል።
ሁለቱ አካላት በኢትዮጵያ የቤላሩስ ባሕል፣ ትምህርት እና ስፖርት ቀን ለማካሄድም ተስማምተዋል።
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮቹ በውይይታቸው በሀገራቱ መሪዎች ደረጃ የሚፈረም የትብብር ፍኖተ ካርታ ለማዘጋጀት መስማማታቸውን የቤላሩስ የሚዲያ አገልግሎት ዘግቧል።