የቤላሩስ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማክሲም ሪዜንኮቭ ለይፋዊ የሥራ ጉብኝት አዲስ አበባ ገቡ
18:53 13.04.2025 (የተሻሻለ: 19:04 13.04.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
የቤላሩስ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማክሲም ሪዜንኮቭ ለይፋዊ የሥራ ጉብኝት አዲስ አበባ ገቡ
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ከኢትዮጵያ አቻቸው ጌዲዮን ጢሞቴዎስ ጋር ውይይት እንደሚያደርጉ የቤላሩስ ፕሬስ አገልግሎት አስታውቋል።
ውይይታቸው በሁለቱ ሀገራት ኢኮኖሚያዊ ግኑኝነት በተለይም በአምራች ኢንዱስትሪው ዘርፍ ስላሉ የትብብር እድሎች ላይ ትኩረቱን እንደሚያደርግ የፕሬስ አገልግሎቱ ጨምሮ ገልጿል።
ሚኒስትሮቹ በቀጣናዊ እና በዓለም አቀፍ ጉዳዩች ዙሪያ ይወያያሉ ተብሎም ይጠበቃል።
የቤላሩስ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር በቆይታቸው ከኢትዮጵያ መንግሥት አመራሮች፣ ሚኒስትሮች እና የንግዱ ማሕበረሰብ ጋር ይወያያሉ ተብሏል።