የአሜሪካ ቀረጥ የአፍሪካን ኢኮኖሚ ሊያናጋ እንደሚችል የአፍሪካ ልማት ባንክ አስጠነቀቀ
12:47 12.04.2025 (የተሻሻለ: 13:04 12.04.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
የአሜሪካ ቀረጥ የአፍሪካን ኢኮኖሚ ሊያናጋ እንደሚችል የአፍሪካ ልማት ባንክ አስጠነቀቀ
የአፍሪካ ልማት ባንክ ፕሬዝዳንት አኪንዊሚ አዴሲና በአቡጃ ባደረጉት ንግግር ስጋቶቹን ዘርዝረዋል፦
47 የአፍሪካ ሀገራት ለከፍተኛ የአሜሪካ ቀረጥ ተጋላጭ ሊሆኑ ይችላሉ።
በውጭ ምንዛሪ ገቢ መቀነስ ምክንያት ደካማ ገንዘቦች ይፈጠራሉ ተብሎ ይጠበቃል።
ከውጭ የሚገቡ ምርቶች ዋጋ ስለሚጨምር የዋጋ ግሽበት ሊያይል ይችላል።
ገቢዎች እየቀነሱ እና የዕዳ ክፍያ በጨመረ ቁጥር የዕዳ ጫና ይፈጠራል።
በዓለም አቀፍ የንግድ ለውጥ ምክንያት የአፍሪካ የኤክስፖርት ምርቶች ፍላጎት በአውሮፓ እና በእስያ ሊቀንስ ይችላል።