ኢኮዋስ አልጄሪያና ማሊ ውጥረታቸውን በውይይት እንዲፈቱ ጥሪ አቀረበ
15:46 10.04.2025 (የተሻሻለ: 16:04 10.04.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ኢኮዋስ አልጄሪያና ማሊ ውጥረታቸውን በውይይት እንዲፈቱ ጥሪ አቀረበ
የምዕራብ አፍሪካ የኢኮኖሚ ማኅበረሰብ (ኢኮዋስ) አልጄሪያና ማሊ ውይይት እንዲያደርጉና ግጭቶቻቸውን በአህጉራዊና ክልላዊ መንገዶች እንዲፈቱ ጠይቋል።
በመጋቢት ወር መጨረሻ የአልጄሪያ ጦር ቲን ዛውአቲን በምትባል የድንበር ከተማ አቅራቢያ የማሊ ሰው አልባ አውሮፕላንን መትቶ መጣሉን ተከትሎ በአልጄሪያና ማሊ መካከል ያለው ዲፕሎማሲያዊ ውጥረት አይሏል።
አልጄሪያ ሰው አልባ አውሮፕላኑ ሉዓላዊነቴን ጥሷል ብላለች። ባማኮ በበኩሏ የአጎራባቿን የአየር ክልል እንዳልጣሰች ገልጻለች።
በክስተቱ ምክንያት ቡርኪናፋሶ፣ ኒጀርና ማሊ አምባሳደሮቻቸውን ከአልጄርስ የጠሩ ሲሆን የአልጄሪያ-ማሊ የአየር ክልል መዘጋትን የመሳሰሉ በርካታ የፖለቲካ ምላሾችን አስከትሏል።
አልጄሪያ የኤኮዋስ አባል አይደለችም። ማሊ በጥር ወር መጨረሻ ከቡድኑ በይፋ ወጥታለች።