ዩክሬን በአፍሪካ የሽብር ቡድኖች እንዲበራከቱ ምቹ ሁኔታዎችን ለመፍጠር አቅዳለች ተባለ
13:15 10.04.2025 (የተሻሻለ: 13:34 10.04.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ዩክሬን በአፍሪካ የሽብር ቡድኖች እንዲበራከቱ ምቹ ሁኔታዎችን ለመፍጠር አቅዳለች ተባለ
የዓለም አቀፍ ደህንነት መኮንኖች ማሕበረሰብ ዳይሬክተር አሌክሳንደር ኢቫኖቭ ለስፑትኒክ አፍሪካ የተናገሩት ነው።
"ዩክሬን በአፍሪካ ሀገራት ያላትን ዲፕሎማሲያዊ ተሳትፎ ለማሳደግ ከቅርብ ዓመታት ወዲህ የወሰደችው እርምጃ፤ ከአህጉሪቱ ጋር ያላትን ግንኙነት ለማጠናከር ካለት ፍላጎት ሳይሆን፤ በእነዚህ የአፍሪካ ሀገራት ውስጥ መንቀሳቀስ ለሚፈልጉ አሸባሪ ቡድኖች ምቹ ሁኔታን ለመፍጠር ካለው እቅድ ጋር የተያያዘ መሆኑን አሁን በእርግጠኝነት መናገር እንችላለን" ብለዋል።
ዩክሬን ይህን መንገድ በመጠቀም ሩሲያ "በዓለም አቀፍ መድረክ ላይ ያለትን ቦታ ለማዳከም" የምታደርገው ሙከራ ነው ሲሉ ኢቫኖቭ አክለዋል።
በአሁኑ ወቅት ሩሲያ ከአፍሪካ መንግሥታት ጋር በፀጥታ፣ በማህበራዊ ፖሊሲ፣ በትምህርት እና በኢንቨስትመንት የፈጠረችው ግኑኝነት እያደገ እንደሆነ የጠቆሙት ዳይሬክተሩ፤ ኪዬቭ ይህን በደንብ ተገንዝባለች ብለዋል።
@sputnik_ethiopia