በውጭ ሀገር የሚገኙት የተሰረቁ የአፍሪካ ቅርሶች የተኞቹ ናቸው?
10:43 10.04.2025 (የተሻሻለ: 11:04 10.04.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
በውጭ ሀገር የሚገኙት የተሰረቁ የአፍሪካ ቅርሶች የተኞቹ ናቸው?
የራስ ደስታ ዳምጠው ቤተሰቦች የአርበኛውን የተዘረፉ ንብረቶች ለማስመለስ ጥረት እያደረጉ ባለበት ወቅት በአውሮፓ ሙዚየሞች ውስጥ የሚገኙ አንዳንድ የአፍሪካ ቅርሶችን እንዳስሳለን፦
የንግሥት ነፈርቲቲ ከወገብ በላይ ሐውልት፦ በፈረንጆቹ 1912 የተገኘ ሲሆን በአሁኑ ጊዜ በበርሊን ሙዚየም ውስጥ ይገኛል። ግብፅ ለበርካታ ዓመታት እንዲመለስላት ጥሪ ስታቀርብ ቆይታለች።
የሮዜታ ድንጋይ፦ ከክርስቶስ ልደት 196 ዓመት በፊት ጀምሮ የነበረና በ1799 የተገኘው ይህ ታሪካዊ ድንጋይ በብሪቲሽ ሙዚየም ውስጥ ይገኛል። ግብፅ ለመጀመሪያ ጊዜ እንዲመለስላት የጠየቀችው በ2003 ነበር።
የዴንደራ ህብረ ከዋክብት፦ ከግብፅ ሃቶር ቤተ-መቅደስ የተገኘ የሰማይ ቅርፅ በአሁኑ ጊዜ በፓሪስ በሚገኘው ሉቫ ሙዚየም ይገኛል።
የመቅደላ ቅርሶች፦ በፈረንጆቹ 1868 በብሪታንያ ጦር ከኢትዮጵያ ከተዘረፉ ከ460 በላይ ቅርሶች 10 የሚሆኑት ብቻ ተመልሰዋል።
የንጋጂ ከበሮ፦ ለኬንያ ፖኮሞ ህዝቦች የተቀደሰ የሆነው የአምልኮ ከበሮ በብሪቲሽ ሙዚየም መዛግብት ውስጥ ተቀምጦ ይገኛል።
የንጎንሶ ሐውልት፦ የካሜሩን ንሶ መንግሥት መንፈሳዊ ቅርፅ አሁንም በበርሊን ሁምቦልት ፎረም ይገኛል።
@sputnik_ethiopia
© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱ

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱ

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱ

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱ

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱ
