በእስራኤል የጋዛ ፖሊሲዎች ዙሪያ የአፍሪካ ሀገራት የሚያሳድሩትን ጫና ጨምረዋል

በእስራኤል የጋዛ ፖሊሲዎች ዙሪያ የአፍሪካ ሀገራት የሚያሳድሩትን ጫና ጨምረዋል
ሰኞ ዕለት አፍሪካ ሕብረት ውስጥ በተካሄደው የሩዋንዳ የዘር ማጥፋት መታሰቢያ ላይ የእስራኤል አምባሳደር መባረራቸውን ተከትሎ በአፍሪካ ሀገራት እና በእስራኤል መካከል ያለው ውጥረት ቀጥሏል። የእስራኤል ዲፕሎማት ከአፍሪካ ሕብረት ስብሰባ ሲባረር ለሁለተኛ ጊዜ ነው።
በርካታ የአፍሪካ ሀገራት በተለይም በጋዛ ያለውን ሁኔታ በተመለከተ በሕጋዊ እርምጃ፣ ዓለም አቀፍ ጥምረት እና በይፋ በማውገዝ የእስራኤልን ድርጊቶች በፅኑ እየተቃወሙ ይገኛሉ። ከዚህ በታች የቅርብ ጊዜ እርምጃዎችን ባጭሩ፦
* ደቡብ አፍሪካ በዓለም አቀፍ ፍርድ ቤት ክሷን ቀጥላለች፦ ፕሪቶሪያ በትራምፕ አስተዳደር የገንዘብ ድጋፍ ቢቋረጥባትም በጋዛ የሚፈጸሙ ጥቃቶችን አስመልክቶ በእስራኤል ላይ ያቀረበችውን የዓለም አቀፍ ፍርድ ቤት ክስ እንደምትቀጥል አረጋግጣለች።
* ለሕጋዊ እርምጃ ሰፊ የአፍሪካ ድጋፍ፦ የደቡብ አፍሪካ ክስ አልጄሪያ፣ ኮሞሮስ፣ ጅቡቲ፣ ግብፅ፣ ሊቢያ፣ ናሚቢያ እና ዚምባብዌ እንዲሁም የአፍሪካ ሕብረት እና የገለልተኛ ሀገራት ንቅናቄን ድጋፍ አግኝቷል።
* "የሄግ ቡድን" የተጠያቂነት ጥረቶችን ማስተባበር፦ ደቡብ አፍሪካ፣ ናሚቢያ እና ሴኔጋልን ጨምሮ ዘጠኝ ሀገራት እስራኤል በጋዛ ውስጥ በምታደርጋቸው ድርጊቶች ተጠያቂ ለማድረግ ጥር 24 ቀን "የሄግ ቡድንን" አቋቁመዋል።
*ፍልስጤማውያንን የማዛወር የደረሰበት ተቃውሞ፦ አሜሪካ እና እስራኤል የተፈናቀሉ ፍልስጤማውያንን ወደ ሱዳን እና ሶማሊያ ለማዛወር ያቀዱት እቅድ ከፍተኛ ተቃውሞ ገጥሞታል።
@sputnik_ethiopia