በእስራኤል የጋዛ ፖሊሲዎች ዙሪያ የአፍሪካ ሀገራት የሚያሳድሩትን ጫና ጨምረዋል

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱበእስራኤል የጋዛ ፖሊሲዎች ዙሪያ የአፍሪካ ሀገራት የሚያሳድሩትን ጫና ጨምረዋል
በእስራኤል የጋዛ ፖሊሲዎች ዙሪያ የአፍሪካ ሀገራት የሚያሳድሩትን ጫና ጨምረዋል - Sputnik አፍሪካ, 1920, 09.04.2025
ሰብስክራይብ

በእስራኤል የጋዛ ፖሊሲዎች ዙሪያ የአፍሪካ ሀገራት የሚያሳድሩትን ጫና ጨምረዋል

ሰኞ ዕለት አፍሪካ ሕብረት ውስጥ በተካሄደው የሩዋንዳ የዘር ማጥፋት መታሰቢያ ላይ የእስራኤል አምባሳደር መባረራቸውን ተከትሎ በአፍሪካ ሀገራት እና በእስራኤል መካከል ያለው ውጥረት ቀጥሏል። የእስራኤል ዲፕሎማት ከአፍሪካ ሕብረት ስብሰባ ሲባረር ለሁለተኛ ጊዜ ነው።

በርካታ የአፍሪካ ሀገራት በተለይም በጋዛ ያለውን ሁኔታ በተመለከተ በሕጋዊ እርምጃ፣ ዓለም አቀፍ ጥምረት እና በይፋ በማውገዝ የእስራኤልን ድርጊቶች በፅኑ እየተቃወሙ ይገኛሉ። ከዚህ በታች የቅርብ ጊዜ እርምጃዎችን ባጭሩ፦

* ደቡብ አፍሪካ በዓለም አቀፍ ፍርድ ቤት ክሷን ቀጥላለች፦ ፕሪቶሪያ በትራምፕ አስተዳደር የገንዘብ ድጋፍ ቢቋረጥባትም በጋዛ የሚፈጸሙ ጥቃቶችን አስመልክቶ በእስራኤል ላይ ያቀረበችውን የዓለም አቀፍ ፍርድ ቤት ክስ እንደምትቀጥል አረጋግጣለች።

* ለሕጋዊ እርምጃ ሰፊ የአፍሪካ ድጋፍ፦ የደቡብ አፍሪካ ክስ አልጄሪያ፣ ኮሞሮስ፣ ጅቡቲ፣ ግብፅ፣ ሊቢያ፣ ናሚቢያ እና ዚምባብዌ እንዲሁም የአፍሪካ ሕብረት እና የገለልተኛ ሀገራት ንቅናቄን ድጋፍ አግኝቷል።

* "የሄግ ቡድን" የተጠያቂነት ጥረቶችን ማስተባበር፦ ደቡብ አፍሪካ፣ ናሚቢያ እና ሴኔጋልን ጨምሮ ዘጠኝ ሀገራት እስራኤል በጋዛ ውስጥ በምታደርጋቸው ድርጊቶች ተጠያቂ ለማድረግ ጥር 24 ቀን "የሄግ ቡድንን" አቋቁመዋል።

*ፍልስጤማውያንን የማዛወር የደረሰበት ተቃውሞ፦ አሜሪካ እና እስራኤል የተፈናቀሉ ፍልስጤማውያንን ወደ ሱዳን እና ሶማሊያ ለማዛወር ያቀዱት እቅድ ከፍተኛ ተቃውሞ ገጥሞታል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

@sputnik_ethiopia

መተግበሪያ | X ላይ ይከተሉን

አዳዲስ ዜናዎች
0