ኢትዮጵያ በብሪክስ ውስጥ የነበራትን የመጀመሪያ ዓመት ቆይታ ገመገመች
19:40 08.04.2025 (የተሻሻለ: 20:14 08.04.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
ኢትዮጵያ በብሪክስ ውስጥ የነበራትን የመጀመሪያ ዓመት ቆይታ ገመገመች
የኢትዮጵያ የብሪክስ ተሳትፎ በሁለተኛው የብሪክስ ፖሊሲ ውይይት ላይ ተገምግሟል።
የኢትዮጵያ የኤክስፐርት ተቋማት የብሪክስ ዕይታዎች ለሀገራዊ ህልሞች ስኬቶች በሚል ሃሳብ በተካሄደው መድረክ ኢትዮጵያ በብሪክስ አባል ሀገራት ሰፊ ገበያ ተጠቃሚ መሆኗን ተሳታፊዎቹ ተናግረዋል።
የውጭ ጉዳይ ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ጃፋር በድሩ በብሔራዊ ደረጃ ምሁራንን ያሳተፈው መድረክ ለብሪክስ አጀንዳ ግብዓት እንደሚሆንና የተሰበሰበው ሀሳብ ለብሪክስ ሀገራት ተወካዮች እንደሚቀርብ ተናግረዋል።
ኢትዮጵያ የብሪክስ አባልነቷ በተለያዩ መስኮች ተጠቃሚነቷን እንዲያረጋግጥ ጠንክራ እየሠራች ትገኛለች።
@sputnik_ethiopia