ሩሲያ እና አፍሪካ በኢነርጂ መስኮች የጋራ ሥራዎችን ለማስተባበር ልዩ የጋራ ጽሕፈት ቤት ስለማቋቋም ተወያዩ
16:44 08.04.2025 (የተሻሻለ: 17:04 08.04.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
ሩሲያ እና አፍሪካ በኢነርጂ መስኮች የጋራ ሥራዎችን ለማስተባበር ልዩ የጋራ ጽሕፈት ቤት ስለማቋቋም ተወያዩ
የሩሲያ ፕሬዝዳንታዊ አማካሪ አንቶን ኮቢያኮቭ እና የአፍሪካ ኢነርጂ ቻምበር ዋና ሥራ አስፈጻሚ ኤንጄ አዩክ ባደረጉት ስብሰባ ተነሳሽነቱን እውን ለማድረግ ሥራዎች መጀመራቸውን የሩሲያውን ሮስኮንግረስ ፋውንዴሽን ጠቅሰው መገናኛ ብዙሃን ዘግበዋል።
የቻምበሩ ዋና ፕሮጀክት የሆነው የአፍሪካ ኢነርጂ ሳምንትን ማስጀመር የስብሰባው ዋና አጀንዳ እንደነበር ዘገባው አክሎ ገልጿል።
ሁለቱ ወገኖች በውይይታቸው በኢነርጂ ዘርፍ በጋራ ለመሥራት ያላቸውን ፍላጎት እንዳረጋገጡና እንደ ሴንት ፒተርስበርግ ዓለም አቀፍ ኢኮኖሚ ፎረም እና የአፍሪካ ኢነርጂ ሳምንት ባሉ ዝግጅቶች ላይ አብረው ለመሥራት ተስማምተዋል።
@sputnik_ethiopia