ሩሲያ እና አፍሪካ በኢነርጂ መስኮች የጋራ ሥራዎችን ለማስተባበር ልዩ የጋራ ጽሕፈት ቤት ስለማቋቋም ተወያዩ
16:44 08.04.2025 (የተሻሻለ: 17:04 08.04.2025)
© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱሩሲያ እና አፍሪካ በኢነርጂ መስኮች የጋራ ሥራዎችን ለማስተባበር ልዩ የጋራ ጽሕፈት ቤት ስለማቋቋም ተወያዩ

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ሩሲያ እና አፍሪካ በኢነርጂ መስኮች የጋራ ሥራዎችን ለማስተባበር ልዩ የጋራ ጽሕፈት ቤት ስለማቋቋም ተወያዩ
የሩሲያ ፕሬዝዳንታዊ አማካሪ አንቶን ኮቢያኮቭ እና የአፍሪካ ኢነርጂ ቻምበር ዋና ሥራ አስፈጻሚ ኤንጄ አዩክ ባደረጉት ስብሰባ ተነሳሽነቱን እውን ለማድረግ ሥራዎች መጀመራቸውን የሩሲያውን ሮስኮንግረስ ፋውንዴሽን ጠቅሰው መገናኛ ብዙሃን ዘግበዋል።
የቻምበሩ ዋና ፕሮጀክት የሆነው የአፍሪካ ኢነርጂ ሳምንትን ማስጀመር የስብሰባው ዋና አጀንዳ እንደነበር ዘገባው አክሎ ገልጿል።
ሁለቱ ወገኖች በውይይታቸው በኢነርጂ ዘርፍ በጋራ ለመሥራት ያላቸውን ፍላጎት እንዳረጋገጡና እንደ ሴንት ፒተርስበርግ ዓለም አቀፍ ኢኮኖሚ ፎረም እና የአፍሪካ ኢነርጂ ሳምንት ባሉ ዝግጅቶች ላይ አብረው ለመሥራት ተስማምተዋል።
@sputnik_ethiopia