ለ30 ዓመታት 'ሀገር አልባ' የነበረችው ሴት በመጨረሻም የደቡብ አፍሪካ ዜግነት ተሰጣት
15:44 08.04.2025 (የተሻሻለ: 16:04 08.04.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ለ30 ዓመታት 'ሀገር አልባ' የነበረችው ሴት በመጨረሻም የደቡብ አፍሪካ ዜግነት ተሰጣት
የ36 ዓመቷ ፕሪምሮዝ ሞዲሳኔ ከዓመታት የቢሮክራሲ ውጣ ውረድ እና በሀገር ውስጥ ጉዳዮች ሚኒስቴር ደርሶብኛል ካለችው በደል በኋላ በመጨረሻም በደቡብ አፍሪካ ፍርድ ቤት ዜግነት ተሰጥቷታል።
ከደቡብ አፍሪካ የዘር ግንድ በዚምባብዌ የተወለደችው የሁለት ልጆች እናት፤ ወላጅ እናቷ ሰነድ አልባ በመሆኗ ምክንያት 'ሀገር አልባ' ሆና ቆይታለች፡፡
የደቡብ አፍሪካ የሀገር ውስጥ ጉዳይ ሚኒስቴር ማመልከቻዋን ቢቃወምም መከላከያ ማቅረብ ባለመቻሉ መታወቂያ እና የልደት የምስክር ወረቀት እንዲሰጣት እንዲሁም የፍርድ ቤት ወጪዋ እንዲከፍላት ፍርድ ቤቱ አዟል።
@sputnik_ethiopia