ሌተናል ጀነራል ታደሰ ወረደ ጌታቸው ረዳን በመተካት የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዘዳንት ሆነው ተሰየሙ
12:20 08.04.2025 (የተሻሻለ: 12:44 08.04.2025)
© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱሌተናል ጀነራል ታደሰ ወረደ ጌታቸው ረዳን በመተካት የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዘዳንት ሆነው ተሰየሙ

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ሌተናል ጀነራል ታደሰ ወረደ ጌታቸው ረዳን በመተካት የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዘዳንት ሆነው ተሰየሙ
የስልጣን ርክክብ ሥነ-ሥርዓቱ የአፍሪካ ሕብረት ሊቀመንበር መሃሙድ አሊ ዩሱፍ፣ የዲፕሎማቲክ ማሕበረሰብ እና ከፍተኛ የመንግሥት ባለስልጣናት በተገኙበት ተካሂዷል፡፡ ጀነራል ታደሰ ላለፉት 2 ዓመታት የአቶ ጌታቸው ምክትል ሆነው አገልግለዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በማህበራዊ ሥሥርር ገፃቸው ባጋሩት ጽሑፍ አዲሱ የክልሉ ፕሬዝዳንት “አሁን ትግራይ ውስጥ ያለውን ክፍተት ሞልተው ወደ ፊት ሊወስዱ ይችላሉ የሚል እምነት በብዙ አካላት የታመነ ነው። የትግራይ ሕዝብ የጠማውን ሰላም እና ልማት፣ እንደ ሌሎች ወንድሞቹ ወጥቶ የመግባት መሻት ስናሳካ፣ ለኢትዮጵያም ለአፍሪካም እጅግ ጠቃሚ የሆነ ነገር ሠርቶ ለማለፍ ታሪክ የሰጣቸውን ዕድል እንደሚጠቀሙበት ተስፋ አደርጋለሁ” ብለዋል፡፡
@sputnik_ethiopia
© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱ

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱ

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱ

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱ

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱ

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱ
