በኢትዮጵያ የኢንዱስትሪ ማሻሻያ ለ5 ሚሊዮን ዜጎች የሥራ እድል መፍጠር መታቀዱን መንግሥት ገለፀ
11:34 08.04.2025 (የተሻሻለ: 15:44 08.04.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
በኢትዮጵያ የኢንዱስትሪ ማሻሻያ ለ5 ሚሊዮን ዜጎች የሥራ እድል መፍጠር መታቀዱን መንግሥት ገለፀ
የኢንዱስትሪ ሚኒስትር ዴኤታ ታረቀኝ ቡልታ አዳዲስ የሥራ እድሎችን መፍጠር እና 17.2 በመቶ የሀገር ውስጥ ምርት ዕድገትን ለማስመዝገብ ያለመ ትልቅ የኢንዱስትሪ ማሻሻያ መጀመሩን ገልፀዋል።
ንግዶችን ማጠናከር፣ ኢንቨስትመንትን መሳብ እና ኢትዮጵያን ወደ ምርት ማዕከልነት መቀየር በመንግሥት የ10 ዓመት እቅድ ውስጥ እንደተካተተም ተናግረዋል፡፡
በተጨማሪም እቅዱ 9 ቢሊዮን የአሜሪካ ዶላር የውጭ ምንዛሪ ገቢ ለማመንጨት እና የኢንዱስትሪ ምርታማነትን በ85 በመቶ ለማሳደግ አንዳለመ ለመንግሥት መገናኛ ብዙሃን አብራርተዋል።
@sputnik_ethiopia