በኢትዮጵያ የእስራኤል አምባሳደር አቭርሃም ንጉሴ ከአፍሪካ ሕብረት ዋና መሥሪያ ቤት ተባረሩ

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱበኢትዮጵያ የእስራኤል አምባሳደር አቭርሃም ንጉሴ ከአፍሪካ ሕብረት ዋና መሥሪያ ቤት ተባረሩ
በኢትዮጵያ የእስራኤል አምባሳደር አቭርሃም ንጉሴ ከአፍሪካ ሕብረት ዋና መሥሪያ ቤት ተባረሩ - Sputnik አፍሪካ, 1920, 07.04.2025
ሰብስክራይብ

በኢትዮጵያ የእስራኤል አምባሳደር አቭርሃም ንጉሴ ከአፍሪካ ሕብረት ዋና መሥሪያ ቤት ተባረሩ

በዛሬው እለት ተካሂዶ በነበረው የሩዋንዳ የዘር ማጥፋት 31ኛ ዓመት መታሰቢያ ላይ ተጋብዘው የነበሩት አምባሳደሩ፤ አባል ሀገራት አሻፈረን በማለታቸው ምክንያት ከአፍሪካ ሕብረት ዋና መሥሪያ ቤት መባረራቸውን የእስራኤል ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታውቋል።

የሚኒስቴሩ ቃል አቀባይ ኦረን ማርሞርስቲን የጅቡቲው የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር ፀረ-እስራኤል የፖለቲካ አካላትን ለማስተናገድ መምረጣቸው በጣም አሳዛኝ ተግባር ነው ብለዋል።

"የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴሩ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመሆን አስፈላጊውን ዲፕሎማሲያዊ እርምጃ ይወስዳል" ሲሉም ተናግረዋል።

@sputnik_ethiopia

መተግበሪያ | X ላይ ይከተሉን

አዳዲስ ዜናዎች
0