በኢትዮጵያ የእስራኤል አምባሳደር አቭርሃም ንጉሴ ከአፍሪካ ሕብረት ዋና መሥሪያ ቤት ተባረሩ
19:57 07.04.2025 (የተሻሻለ: 20:14 07.04.2025)
© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱበኢትዮጵያ የእስራኤል አምባሳደር አቭርሃም ንጉሴ ከአፍሪካ ሕብረት ዋና መሥሪያ ቤት ተባረሩ

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
በኢትዮጵያ የእስራኤል አምባሳደር አቭርሃም ንጉሴ ከአፍሪካ ሕብረት ዋና መሥሪያ ቤት ተባረሩ
በዛሬው እለት ተካሂዶ በነበረው የሩዋንዳ የዘር ማጥፋት 31ኛ ዓመት መታሰቢያ ላይ ተጋብዘው የነበሩት አምባሳደሩ፤ አባል ሀገራት አሻፈረን በማለታቸው ምክንያት ከአፍሪካ ሕብረት ዋና መሥሪያ ቤት መባረራቸውን የእስራኤል ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታውቋል።
የሚኒስቴሩ ቃል አቀባይ ኦረን ማርሞርስቲን የጅቡቲው የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር ፀረ-እስራኤል የፖለቲካ አካላትን ለማስተናገድ መምረጣቸው በጣም አሳዛኝ ተግባር ነው ብለዋል።
"የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴሩ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመሆን አስፈላጊውን ዲፕሎማሲያዊ እርምጃ ይወስዳል" ሲሉም ተናግረዋል።
@sputnik_ethiopia