የዋሊያ አይቤክስ ቁጥርን ለመመለስ እና ለማሣደግ ያለመ ስትራቴጂካዊ ዕቅድ ተዘጋጀ
19:38 07.04.2025 (የተሻሻለ: 20:04 07.04.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
የዋሊያ አይቤክስ ቁጥርን ለመመለስ እና ለማሣደግ ያለመ ስትራቴጂካዊ ዕቅድ ተዘጋጀ
ዕቅዱ የዋሊያ አይቤክስን ደኅንነት ለመታደግ ያለመ ውይይት በጎንደር ከተማ በተካሄደበት ወቅት ይፋ ሆኗል።
በሺዎች ይቆጠር የነበረው ዋልያ አይቤክስ ወደ 300 ዝቅ ማለቱን የኢትዮጵያ የዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን በቅርቡ ማስታወቁ ይታወሳል።
ስትራቴጂካዊ ዕቅዱ ኃላፊነት ያለባቸው አካላት ተቀናጅተው በመሥራት የሀገር ምልክት የኾነውን ዋሊያ አይቤክስ ከተጋረጠበት አደጋ እንዲከላከሉ የሚያስችላቸው ነው ተብሏል።
@sputnik_ethiopia