ሩሲያ እና የሳህል ጥምረት በሰላምና ደህንነት ጉዳዮች ላይ ትብብራቸውን እንደሚያጠናክሩ የማሊ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ገለፁ
18:09 07.04.2025 (የተሻሻለ: 18:14 07.04.2025)
© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
ሩሲያ እና የሳህል ጥምረት በሰላምና ደህንነት ጉዳዮች ላይ ትብብራቸውን እንደሚያጠናክሩ የማሊ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ገለፁ
"ውይይታችን ቀጥተኛ እና ግልጽ ነበር። ሩሲያ ከእኛ ጋር መሥራቷን ለመቀጠል እና በነዚህ ጉዳዮች ላይ ያላትን ሁለገብ ትብብር ለማጠናከር ጠንካራ ቁርጠኝነት አይተናል” ሲሉ የሩሲያ እና የሳህል ጥምረት ሀገራት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች በሞስኮ ከተገናኙ በኋላ ከስፑትኒክ በነበራቸው ቃለ ምልልስ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ አብዱላዬ ዲዮፕ ተናግረዋል፡፡
የሳህል ሀገራት ጥምረት ሩሲያ አሁን "የምናካሂዳቸውን የጋራ ወታደራዊ እንቅስቃሴዎች በመደገፍ የኮንፌዴሬሽኑን ጥረቶች ትረዳለች ብሎ ይጠበቃል" ሲሉ ሚኒስትሩ አክለዋል፡፡
የኮንፌዴሬሽኑ የረጅም ጊዜ ግብ የደህንነት ስጋቶችን ለመቅረፍ "የተዋሃደ የሳህል ኃይል" መፍጠር እንደሆነም ሚኒስትሩ ጨምረው ገልጸዋል።
@sputnik_ethiopia