አፍሪካ በአሜሪካ ቀረጥ ምክንያት አህጉራዊውን ነፃ የንግድ ቀጣና ማጠናከር አለባት ሲሉ የናይጄሪያ ሚኒስትር ተናገሩ

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱአፍሪካ በአሜሪካ ቀረጥ ምክንያት አህጉራዊውን ነፃ የንግድ ቀጣና ማጠናከር አለባት ሲሉ የናይጄሪያ ሚኒስትር ተናገሩ
አፍሪካ በአሜሪካ ቀረጥ ምክንያት አህጉራዊውን ነፃ የንግድ ቀጣና ማጠናከር አለባት ሲሉ የናይጄሪያ ሚኒስትር ተናገሩ - Sputnik አፍሪካ, 1920, 07.04.2025
ሰብስክራይብ

አፍሪካ በአሜሪካ ቀረጥ ምክንያት አህጉራዊውን ነፃ የንግድ ቀጣና ማጠናከር አለባት ሲሉ የናይጄሪያ ሚኒስትር ተናገሩ

አዲሱ የአሜሪካ ቀረጥ ወሳኝ የናይጄሪያ ምርቶች በአሜሪካ ገበያ ያላቸውን ተወዳዳሪነት ሊጎዳ ይችላል ሲሉ የናይጄሪያ የኢንዱስትሪ፣ ንግድና ኢንቨስትመንት ሚኒስትር ጁሞኬ ኦዱዎሌ ተናግረዋል።

በዚህም ናይጄሪያ የኢኮኖሚዋን የመቋቋም አቅም ለማጠናከር እና የወጪ ንግዷን ማብዛት ትፈልጋልች ሲሉ ሚኒስትሯ ገልጸዋል።

ናይጄሪያ እየጨመረ የመጣውን ክልላዊ እና ዓለም አቀፍ ቀረጥ በመቋቋም የሀገር ውስጥ ንግዶችን ተወዳዳሪነት ለማሳደግ እንዲሁም ኢንቨስትመንትን ለመሳብ እና ለማቆየት ፖሊሲዎችን፣ የገንዘብ፣ የመሠረተ ልማት እና ዲፕሎማሲያዊ እርምጃዎችን እየወሰደች ነው ብለዋል።

ባለፉት ሁለት ዓመታት ናይጄሪያ ወደ አሜሪካ የምትለከው ዓመታዊ ምርት ከ5-6 ቢሊዮን ዶላር ገደማ ነበር። ከዚህ ወስጥ 90 በመቶው የኃይል ዘርፉ እንደሚሸፍነውና አሜሪካ ለናይጄሪያ ወሳኝ የንግድ እና የኢንቨስትመንት አጋር እንደሆነች ሚኒስትሯ ጨምረው ገልጸዋል።

ምስሉ በሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) የተሠራ ነው

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

@sputnik_ethiopia

መተግበሪያ | X ላይ ይከተሉን

አዳዲስ ዜናዎች
0