በሩዋንዳ ቱትሲዎች ላይ የተፈፀመው የዘር ጭፍጨፋ 31ኛ ዓመት መታሰቢያ በአዲስ አበባ ተካሄደ
16:36 07.04.2025 (የተሻሻለ: 16:54 07.04.2025)
© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱበሩዋንዳ ቱትሲዎች ላይ የተፈፀመው የዘር ጭፍጨፋ 31ኛ ዓመት መታሰቢያ በአዲስ አበባ ተካሄደ

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
በሩዋንዳ ቱትሲዎች ላይ የተፈፀመው የዘር ጭፍጨፋ 31ኛ ዓመት መታሰቢያ በአዲስ አበባ ተካሄደ
የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር ማሃሙድ አሊ የሱፍ በመርሃ ግብሩ ላይ ባደረጉት ንግግር "በአፍሪካ ተመሳሳይ አይነት ጥፋት የትም እና መቼም እንዳይደገም ግጭትን ቀድሞ ለማስቀረት የሚያስችሉ አቅሞችን ሕብረቱ እንዲፈጥር ማድረግ ወሳኝ ነው” ብለዋል፡፡
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ብርቱካን አያኖ መታሰቢያው በጭፍጨፋው ሕይወታቸውን ያጡ ንፁሃን ዜጎች የሚታወሱበት ብቻ ሳይሆን የሩዋንዳውያን ፅናት እውቅና የሚሰጥበት እንደሆነ ተናግረዋል፡፡ ሩዋንዳ አስከፊውን ምዕራፍ ተሻግራ በይቅርታ፣ እርቅ እና በሀገር መልሶ ግንባታ ዛሬ ላይ ተምሳሌታዊ መሆን መቻሏንም ገልጸዋል።
በኢትዮጵያ የሩዋንዳ አምባሳደር ቻርልስ ካራምባ በበኩላቸው በዘር ጭፍጨፋ ማግስት በሩዋንዳ ሰላም እና መረጋጋትን ለማስፋን ቀዳሚ ከሆኑ ሀገራት ኢትዮጵያ ዋነኛዋ እንደነበረች በመግለፅ ምስጋና አቅርበዋል።
@sputnik_ethiopia
© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱ

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱ

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱ

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱ

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱ
