ታላቁ የህዳሴ ግድብ የቀጣናውን ሀገራት በጋራ የማደግ ራዕይ የሚያሳካ ፕሮጀክት ነው ሲሉ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ተናገሩ
20:54 06.04.2025 (የተሻሻለ: 21:14 06.04.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
ታላቁ የህዳሴ ግድብ የቀጣናውን ሀገራት በጋራ የማደግ ራዕይ የሚያሳካ ፕሮጀክት ነው ሲሉ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ተናገሩ
የህዳሴ ግድብ አፍሪካን በንግድና ኢንቨስትመንት በማስተሳሰር አህጉራዊ የኢኮኖሚ ውህደትን ለመፍጠር በሚደረገው ጥረት ጉልህ አስተዋጽኦ እንደሚኖረው ቃል አቀባዩ አምባሳደር ነብያት ጌታቸው ተናግረዋል።
የግድቡ ግንባታ በርካታ ፈተናዎች ማለፉን ያነሱት ቃል አቀባዩ የታችኛው ተፋሰስ ሀገራት ጫና ለመፍጠር የግድቡን ጉዳይ ዓለም አቀፍ ለማድረግ መሞከራቸውን አስታውሰዋል።
ታላቁ የህዳሴ ግድብ ከኢትዮጵያውያን አልፎ ለአፍሪካውያንም በራስ አቅም ታላላቅ አህጉራዊ ፕሮጀክቶችን መገንባት እንደሚቻል መነሳሳትን የፈጠረ ፕሮጀክት ነው ማለታቸውን ጠቅሶ የሀገር ውስጥ ሚዲያ ነው የዘገበው።
@sputnik_ethiopia