ዚምባብዌ የትራምፕን ቀረጥ ተከትሎ በአሜሪካ ምርቶች ላይ የምትጥለውን ቀረጥ ልታነሳ ነው
20:16 06.04.2025 (የተሻሻለ: 20:34 06.04.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ዚምባብዌ የትራምፕን ቀረጥ ተከትሎ በአሜሪካ ምርቶች ላይ የምትጥለውን ቀረጥ ልታነሳ ነው
የዚምባብዌ ፕሬዝዳንት ኤመርሰን ምናንጋግዋ እርምጃው ከአሜሪካ ወደ ዚምባብዌ የሚገቡ እና ከዚምባብዌ ወደ አሜሪካ የሚላኩ ምርቶችን ለመጨመር ያለመ ነው ብለዋል።
የአፀፋ ቀረጥ የራሱ ጥቅም ቢኖረውም ዚምባቡዌ ከሌሎች ሀገራት ጋር መፍጠር ከምትፈልገው የወዳጅነት ግንኙነት አንጻር ቀዳሚ መሆን የለበትም ብለዋል።
የፖሊሲ ለውጡ ትራምፕ መጋቢት 24 ቀን በዚምባብዌ ምርቶች ላይ 18 በመቶ ቀረጥ መጣላቸውን ተከትሎ የመጣ ነው። በአፍሪካ ሀገራት ላይ የተጣለው አዲሱ ቀረጥ ከ10 በመቶ እስከ 50 በመቶ ይደርሳል።
@sputnik_ethiopia