የቶጎ ፕሬዝዳንት በኮንጎ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ግጭት ዙሪያ የሚካሄደውን ሽምግልና እንዲመሩ በአፍሪካ ሕብረት ተመረጡ
19:01 06.04.2025 (የተሻሻለ: 19:24 06.04.2025)
© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱየቶጎ ፕሬዝዳንት በኮንጎ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ግጭት ዙሪያ የሚካሄደውን ሽምግልና እንዲመሩ በአፍሪካ ሕብረት ተመረጡ

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
የቶጎ ፕሬዝዳንት በኮንጎ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ግጭት ዙሪያ የሚካሄደውን ሽምግልና እንዲመሩ በአፍሪካ ሕብረት ተመረጡ
የአፍሪካ ሕብረት የወቅቱ ሊቀመንበር ጃኦ ሎሬንሶ የቶጎ ፕሬዝዳንት ፋር ግናሲንግቤ ሹመቱን እንደተቀበሉ ተናግረዋል።
የአፍሪካ ሕብረት ኃላፊነታቸው ላይ ትኩረት ለማድረግ ከአሸማጋይነታቸው በቅርቡ ያገለሉት ሎሬንሶ፤ በምስራቅ ኮንጎ እየተባባሰ የመጣው የሰብዓዊ ቀውስ አሳሳቢና ለቀጣናው መረጋጋት ስጋት ነው ብለዋል።
የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር ሞሐመድ አሊ ዩሱፍ የሰላም ድርድሩ ፍኖተ ካርታ በጥልቅ መታየት አለበት ሲሉ አፅንኦት ሰጥተዋል።
የግናሲንግቤ ሹመት ከፀደቀ በኋላ በደቡብ አፍሪካ የልማት ማሕበረሰብ እና በምስራቅ አፍሪካ ማሕበረሰብ ከሚመረጡ አምስት አስተባባሪዎች ጋር በጋራ እንደሚሠሩ ተገልጿል።
@sputnik_ethiopia