ሩሲያ አዲሱ የአሜሪካ ቀረጥ አይመለከታትም ሲል ክሬምሊን ገለፀ
17:33 04.04.2025 (የተሻሻለ: 18:04 04.04.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ሩሲያ አዲሱ የአሜሪካ ቀረጥ አይመለከታትም ሲል ክሬምሊን ገለፀ
በአጠቃላይ አዲሱ የአሜሪካ ቀረጥ የሚያስከትለው መዘዝ ሩሲያን አይጠቅምም ሲሉ የክሬምሊን ቃል አቀባይ ዲሚትሪ ፔስኮቭ ተናግረዋል።
የክሬምሊን ቃል አቀባይ ዲሚትሪ ፔስኮቭ የአሜሪካን ቀረጥ በተመከተ ከሰጡት መግለጫ የተወሰዱ ቁልፍ ነጥቦች፡-
▪ሩሲያ አሜሪካ ያስተዋወቀችው አዲስ ቀረጥ በኢኮኖሚዋ ላይ ሊያስከትል የሚችለውን ጉዳት ለመቀነስ መጠንቀቅ አለባት።
▪የሩሲያ ኢኮኖሚ ጠንካራ እና እያደገ ያለ ቢሆንም የዓለም ሁኔታ ተለዋዋጭ በመሆኑ ምክንያት ተጨማሪ እርምጃዎች ይወሰዳሉ።
▪በፑቲን እና በትራምፕ መካከል በመጪዎቹ ቀናት ውስጥ የታቀደ የስልክ ውይይት የለም።
▪ሩሲያ ከአሜሪካ ጋር ያላትን ግንኙነት ወደነበረበት ለመመለስ እየሠራች ነው።
▪በሩሲያ እና በአሜሪካ መካከል በሚደረገው የውይይት የጦር መሳሪያ ቁጥጥር አጀንዳ መሆን አለበት። ነገር ግን እስካሁን በተደረጉ ንግግሮች አጀንዳው አልተነሳም።
▪የዩክሬን የፀጥታ ዋስትና ጉዳይ የድርድር አጀንዳ ነው። እስካሁን ዝርዝር ጉዳይ የለም።
▪የሩሲያ ልዩ መልዕክተኛ ኪሪል ዲሚትሪቭ በዋሽንግተን ያደረጉት ውይይት በጣም ወሳኝ እና የሚቀጥል ይሆናል።
@sputnik_ethiopia