ኢትዮጵያ የቤት ሠራተኞችን የጡረታ ተከፋይ የሚያደርግ ሕግ ልታፀድቅ ነው
15:02 04.04.2025 (የተሻሻለ: 15:24 04.04.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
ኢትዮጵያ የቤት ሠራተኞችን የጡረታ ተከፋይ የሚያደርግ ሕግ ልታፀድቅ ነው
ደንቡ የቤት ሠራተኞችን የማሕበራዊ አግልግሎት ተጠቃሚ የሚያደርግ ነው። በሥራ እና ክህሎት ሚኒስቴር የተዘጋጀው ረቂቅ ደንብ በሚቀጥሉት ስድስት ወራት ይፀድቃል ተብሎ እንደሚጠበቅ የሀገር ውስጥ ሚዲያ ዘግቧል።
ደንቡ በዋናነት ወጥ እና ሕጋዊ ተቀባይነት ያለው እና ሠራተኛውን እና አሠሪውን ተጠቃሚ የሚያደርግ ውል የመፍጠር ዓላማ አለው።
ደንቡ ሥራ ላይ ሲውል የቤት ሠራተኞች የሕክምና አገልግሎት እና ጡረታን ጨምር የማሕበራዊ ዋስትና ጥቅሞችን እንዲያገኙ የሚፈቅድ እንደሆነ ተነግሯል።
@sputnik_ethiopia