ኢትዮጵያ የሰቆጣ ቃልኪዳን ትግበራን በ334 ወረዳዎች አስፋፋች
20:26 03.04.2025 (የተሻሻለ: 20:54 03.04.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ኢትዮጵያ የሰቆጣ ቃልኪዳን ትግበራን በ334 ወረዳዎች አስፋፋች
የኢትዮጵያ የምግብ እና ስርዓተ ምግብ ትራንስፎርሜሽን የሚኒስትሮች ስቲሪንግ ኮሚቴ የስድት ወር አፈጻጸም ግምገማ መድረክ ተካሂዷል። በመድረኩ ላይ ንግግር ያደረጉት የጤና ሚኒስትር ዶ/ር መቅደስ ዳባ ፕሮግራሙን ተደራሽ ለማድረግ የመንግሥትና የአጋሮችን ድጋፍ በማስተባበር እየተሠራ መሆኑን ተናግረዋል።
በመድረኩ በሰቆጣ ቃልኪዳን የስድት ወር አፈጻጸም ሪፖርት ላይ ሰፊ ውይይት እንደተደረገ የጤና ሚኒስቴር በማህበራዊ የትሥሥር ገፁ አስነብቧል።
በ2007 ዓ.ም የተፈረመው የሰቆጣ ቃልኪዳን ከሁለት ዓመት በታች ያሉ ህፃናትን ከመቀንጨር ለመከላከል ወጥኖ የተነሳ ነው። ቃልኪዳኑ ከ7.8 ሚሊዮን በላይ የሚሆኑ ሕጻናትን በ15 ዓመት ውስጥ ከመቀንጨር ለመታደግ ያቀደ ነው።
@sputnik_ethiopia