ኢትዮጵያ የሰቆጣ ቃልኪዳን ትግበራን በ334 ወረዳዎች አስፋፋች

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱኢትዮጵያ የሰቆጣ ቃልኪዳን ትግበራን በ334 ወረዳዎች አስፋፋች
ኢትዮጵያ የሰቆጣ ቃልኪዳን ትግበራን በ334 ወረዳዎች አስፋፋች - Sputnik አፍሪካ, 1920, 03.04.2025
ሰብስክራይብ

ኢትዮጵያ የሰቆጣ ቃልኪዳን ትግበራን በ334 ወረዳዎች አስፋፋች

የኢትዮጵያ የምግብ እና ስርዓተ ምግብ ትራንስፎርሜሽን የሚኒስትሮች ስቲሪንግ ኮሚቴ የስድት ወር አፈጻጸም ግምገማ መድረክ ተካሂዷል። በመድረኩ ላይ ንግግር ያደረጉት የጤና ሚኒስትር ዶ/ር መቅደስ ዳባ ፕሮግራሙን ተደራሽ ለማድረግ የመንግሥትና የአጋሮችን ድጋፍ በማስተባበር እየተሠራ መሆኑን ተናግረዋል።

በመድረኩ በሰቆጣ ቃልኪዳን የስድት ወር አፈጻጸም ሪፖርት ላይ ሰፊ ውይይት እንደተደረገ የጤና ሚኒስቴር በማህበራዊ የትሥሥር ገፁ አስነብቧል።

በ2007 ዓ.ም የተፈረመው የሰቆጣ ቃልኪዳን ከሁለት ዓመት በታች ያሉ ህፃናትን ከመቀንጨር ለመከላከል ወጥኖ የተነሳ ነው። ቃልኪዳኑ ከ7.8 ሚሊዮን በላይ የሚሆኑ ሕጻናትን በ15 ዓመት ውስጥ ከመቀንጨር ለመታደግ ያቀደ ነው።

@sputnik_ethiopia

መተግበሪያ | X ላይ ይከተሉን

አዳዲስ ዜናዎች
0