የፓን አፍሪካ ወጣት አመራሮች ጉባኤ በኢትዮጵያ መካሄድ ጀመረ

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱየፓን አፍሪካ ወጣት አመራሮች ጉባኤ በኢትዮጵያ መካሄድ ጀመረ
የፓን አፍሪካ ወጣት አመራሮች ጉባኤ በኢትዮጵያ መካሄድ ጀመረ - Sputnik አፍሪካ, 1920, 03.04.2025
ሰብስክራይብ

የፓን አፍሪካ ወጣት አመራሮች ጉባኤ በኢትዮጵያ መካሄድ ጀመረ

ጉባኤው "የወጣቶችን አቅም - ለበለፀገች አፍሪካ" በሚል መሪ ሃሳብ ከመጋቢት 25 እስከ 27 ድረስ አዲስ አበባ በሚገኘው የዓድዋ ድል መታሰቢያ ሙዚየም ይካሄዳል፡፡

በጉባኤው የመክፈቻ ሥነ-ሥርዓት ላይ ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀስላሴ፣ የሴቶችና እና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር ኤርጎጌ ተስፋዬ፣ የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሀት ካሚል፣ የከተማና መሠረተ ልማት ሚኒስትር ጫልቱ ሳኒ እና ሌሎችም ከፍተኛ የመንግሥት ባለስልጣናት ተገኝተዋል።

ከሁሉም የአፍሪካ ሀገራት የተውጣጡ ወጣት አመራሮች፣ የወጣት ሚኒስትሮች፣ የማህበረሰብ መሪዎች፣ ተፅዕኖ ፈጣሪ ግለሰቦችና ሌሎችም የጉባኤው ተሳታፊ ናቸው።

በጉባኤው የጅቡቲ፣ የደቡብ አፍሪካ፣ የኬኒያ፣ የአልጄሪያ፣ የብሩንዲ እና የቦትሶዋና ተወካዮች  እንደሚሳተፉ በስፍራው ላይ የሚገኘው የስፑትኒክ አፍሪካ ጋዜጠኛ ዘግቧል።

@sputnik_ethiopia

መተግበሪያ | X ላይ ይከተሉን

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱ
የፓን አፍሪካ ወጣት አመራሮች ጉባኤ በኢትዮጵያ መካሄድ ጀመረ - Sputnik አፍሪካ
1/2
© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱ
የፓን አፍሪካ ወጣት አመራሮች ጉባኤ በኢትዮጵያ መካሄድ ጀመረ - Sputnik አፍሪካ
2/2
1/2
2/2
አዳዲስ ዜናዎች
0