ትምህርት ሚኒስቴር የዩኒቨርስቲ ተማሪዎች ለአንድ ዓመት እንዲያስተምሩ የሚያስገድድ አሠራር ተግባራዊ ለማድረግ ማቀዱን ይፋ አደረገ

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱትምህርት ሚኒስቴር የዩኒቨርስቲ ተማሪዎች ለአንድ ዓመት እንዲያስተምሩ የሚያስገድድ አሠራር ተግባራዊ ለማድረግ ማቀዱን ይፋ አደረገ
ትምህርት ሚኒስቴር የዩኒቨርስቲ ተማሪዎች ለአንድ ዓመት እንዲያስተምሩ የሚያስገድድ አሠራር ተግባራዊ ለማድረግ ማቀዱን ይፋ አደረገ - Sputnik አፍሪካ, 1920, 03.04.2025
ሰብስክራይብ

ትምህርት ሚኒስቴር የዩኒቨርስቲ ተማሪዎች ለአንድ ዓመት እንዲያስተምሩ የሚያስገድድ አሠራር ተግባራዊ ለማድረግ ማቀዱን ይፋ አደረገ

"የኢትዮጵያ ዩኒቨርስቲ ሰርቪስ'' የሚል መጠሪያ የተሰጠው አሠራር ከ2019 ዓ.ም ጀምሮ ሥራ ላይ እንዲውል ታቅዷል፡፡

የትምህርት ሚኒስትር ብርሃኑ ነጋ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ቀርበው በሰጡት ማብራሪያ አሠራሩ በሀገሪቱ ያለውን የመምህራን ዕጥረት እንደሚቀርፍ አስረድተዋል። በሀገሪቱ 100 ሺህ የሚደርስ የመምህራን ዕጥረት መኖሩን በተደረገ ግምገማ መታወቁን ተናግረዋል፡፡

በአሠራሩ መሠረት በአራት ዓመት የሚመረቅ ተማሪ የሦስተኛ ዓመት ትምህርቱን እንዳጠናቀቀ ወደ አስተማረው ማኅበረሰበብ ተመልሶ ለአንድ ዓመት የማስተማር አገልግሎት ከሰጠ በኋላ እንደሚመረቅ ተገልጿል፡፡

ሙያው ላይ የሚታየውን ክፍተት ለማስተካከል መምህራን በሀገሪቱ የፋይናንስ ሥርዓት ውስጥ የራሳቸው ድርሻ እንዲኖራቸውና የኑሮ ውድነቱን እንዲቋቋሙ ለማድረግ "የመምህራን ባንክ" ለማቋቋም ታቅዷል፡፡

@sputnik_ethiopia

መተግበሪያ | X ላይ ይከተሉን

አዳዲስ ዜናዎች
0