የትራምፕ አስተዳደር ዩኤስኤአይዲን ለማፍረስ በሚያደረገው የመጨረሻ ጥረት ሁሉንም የውጭ ሀገር ሠራተኞች እና ዲፕሎማቶች ሊያባርር አንደሆነ አንድ ሪፖርት አመላከተ
16:27 02.04.2025 (የተሻሻለ: 16:44 02.04.2025)
© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱየትራምፕ አስተዳደር ዩኤስኤአይዲን ለማፍረስ በሚያደረገው የመጨረሻ ጥረት ሁሉንም የውጭ ሀገር ሠራተኞች እና ዲፕሎማቶች ሊያባርር አንደሆነ አንድ ሪፖርት አመላከተ

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
የትራምፕ አስተዳደር ዩኤስኤአይዲን ለማፍረስ በሚያደረገው የመጨረሻ ጥረት ሁሉንም የውጭ ሀገር ሠራተኞች እና ዲፕሎማቶች ሊያባርር አንደሆነ አንድ ሪፖርት አመላከተ
የአሜሪካ የተራድኦ ድርጅት (ዩኤስኤአይዲ) የሰው ሀብት ቢሮ ከ10 ሺህ በላይ የውጭ ዜጎች እና 600 የሚሆኑ የአሜሪካ ዲፕሎማቶች የሥራ ስንብት ማስታወቂያ እንደሚደርሳቸውና ስንብቱ ከነሃሴ ጀምሮ ተግባራዊ እንደሚሆን ማሳወቁን ለጉዳዩ ቅርብ የሆኑ ሰዎቸን ጠቅሶ የእንግሊዝ ሚዲያ ዘግቧል፡፡
በዘገባው የተጠቀሱ የቀድሞ የዩኤስኤአይዲ ከፍተኛ ባለስልጣን "ይህ በእውነትም ማብቂያው ነው" ብለዋል።
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማርኮ ሩቢዮ ተቋማቸው የተወሰኑ የዩኤስኤአይዲ ተግባራትን ለመረከብ እና ቀሪውን እስከ ሰኔ 24 ድረስ ለማቆም እንዳቀደ ባሳለፍነው አርብ ለኮንግረስ ተናግረዋል።
ከሩቢዮ መግለጫ በኋላ በሺዎች የሚቆጠሩ የዩኤስኤአይዲ ሠራተኞች የሥራ ስንብት ደብዳቤ ደርሷቸዋል። የትራምፕ አስተዳደር እየጨመረ የመጣውን የመንግሥት በጀት አለመመጣጠን ለመቀነስ ከ5 ሺህ በላይ ፕሮግራሞችን አቋርጧል።
@sputnik_ethiopia