የቻይና ቤልት ኤንድ ሮድ ኢኒሼቲቭ የኢትዮጵያን የንግድ ማዕከልነት አሳድጓል ሲሉ በቻይና የኢትዮጵያ አምባሳደር ተናገሩ

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱየቻይና ቤልት ኤንድ ሮድ ኢኒሼቲቭ የኢትዮጵያን የንግድ ማዕከልነት አሳድጓል ሲሉ በቻይና የኢትዮጵያ አምባሳደር ተናገሩ
የቻይና ቤልት ኤንድ ሮድ ኢኒሼቲቭ የኢትዮጵያን የንግድ ማዕከልነት አሳድጓል ሲሉ በቻይና የኢትዮጵያ አምባሳደር ተናገሩ - Sputnik አፍሪካ, 1920, 02.04.2025
ሰብስክራይብ

የቻይና ቤልት ኤንድ ሮድ ኢኒሼቲቭ የኢትዮጵያን የንግድ ማዕከልነት አሳድጓል ሲሉ በቻይና የኢትዮጵያ አምባሳደር ተናገሩ

ከመንግሥት ጋዜጣ ጋር ቃለ ምልልስ የነበራቸው በቻይና የኢትዮጵያ አምባሳደር ተፈራ ደርበው የቤልት ኤንድ ሮድ ኢንሼቲቭ ከጅማሮው ጀምሮ የኢትዮጵያን እድገት እና ዘመናዊነት በማፋጠን ረገድ ትልቅ አስተዋጽኦ እንደነበረው ተናግረዋል።

ለአብነትም ቻይና በአዲስ አበባ-ጅቡቲ የባቡር መስመር፣ በመንገድ ዝርጋታ፣ በኢንዱስትሪ ፓርኮች እና ሌሎች ቁልፍ የመሠረተ ልማት ፕሮጀክቶች ላይ መወዕለ ነዋይ እንዳፈሰሰች አንስተዋል።

በተጨማሪም ፕሮጀክቱ ለኢትዮጵያ የኢነርጂ፣ የግብርና እና የማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ እድገት ድጋፍ አድርጓል ብለዋል።

"በአጠቃላይ ይህ ተነሳሽነት የኢትዮጵያን የንግድ እና የኢንቨስትመንት ቀጣናዊ ማዕከልነት በማጠናከር ለሀገሪቱ እድገት እና ዘመናዊነት አስተዋፅኦ እያበረከተ ነው ሲሉ" ተናግረዋል።

እ.አ.አ 2013 በፕሬዝዳንት ሺ ጂንፒንግ ይፋ የተደረገው የቤልት ኤንድ ሮድ ኢኒሼቲቭ፤ የመሠረተ ልማት ጉድለቶችን በመሙላት በእስያ ፓሲፊክ፣ አፍሪካ እንዲሁም በማዕከላዊ እና ምስራቅ አውሮፓ የኢኮኖሚ እድገት የማፋጠን ዓላማ አንግቧል።

@sputnik_ethiopia

መተግበሪያ | X ላይ ይከተሉን

አዳዲስ ዜናዎች
0