ኢትዮጵያ በአዲሱ የተመድ የዲጂታል እና የሰው ሰራሽ አስተውሎት ፕሮግራም ላይ በንቃት እንድትሳተፍ ጥሪ ቀረበላት
13:19 02.04.2025 (የተሻሻለ: 13:34 02.04.2025)
© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱኢትዮጵያ በአዲሱ የተመድ የዲጂታል እና የሰው ሰራሽ አስተውሎት ፕሮግራም ላይ በንቃት እንድትሳተፍ ጥሪ ቀረበላት

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ኢትዮጵያ በአዲሱ የተመድ የዲጂታል እና የሰው ሰራሽ አስተውሎት ፕሮግራም ላይ በንቃት እንድትሳተፍ ጥሪ ቀረበላት
ጥሪው የቀረበው የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቴዎስ ከተመድ ረዳት ዋና ፀሐፊ እና የዲጂታልና አዲስ ቴክኖሎጂ ልዩ መልዕክተኛ ጋር በተወያዩበት ወቅት ነው።
አዲሱ የተመድ የዲጂታልና የአዲስ ቴክኖሎጂዎች ፕሮግራም በሰው ሰራሽ አስተውሎት ዙሪያ ወጥ የሆነ አስተዳደር ለማውጣት እና የአቅም ግንባት ሥራዎችን ለመሥራት የተቋቋመ እንደሆነ ዋና ፀሐፊው በውይይቱ ላይ አስታውቀዋል።
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ኢትዮጵያ ለቴክኖሎጂ ዘርፉ ትኩረት ሰጥታ እየሠራች እንደሆነ በመጠቆም በተመድ ፕሮግራም ላይ በንቃት እንደምትሳተፍ መግለፃቸውን ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የተገኘው መረጃ ያሳያል።
@sputnik_ethiopia