ኢትዮጵያ በአዲሱ የተመድ የዲጂታል እና የሰው ሰራሽ አስተውሎት ፕሮግራም ላይ በንቃት እንድትሳተፍ ጥሪ ቀረበላት
13:19 02.04.2025 (የተሻሻለ: 13:34 02.04.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
ኢትዮጵያ በአዲሱ የተመድ የዲጂታል እና የሰው ሰራሽ አስተውሎት ፕሮግራም ላይ በንቃት እንድትሳተፍ ጥሪ ቀረበላት
ጥሪው የቀረበው የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቴዎስ ከተመድ ረዳት ዋና ፀሐፊ እና የዲጂታልና አዲስ ቴክኖሎጂ ልዩ መልዕክተኛ ጋር በተወያዩበት ወቅት ነው።
አዲሱ የተመድ የዲጂታልና የአዲስ ቴክኖሎጂዎች ፕሮግራም በሰው ሰራሽ አስተውሎት ዙሪያ ወጥ የሆነ አስተዳደር ለማውጣት እና የአቅም ግንባት ሥራዎችን ለመሥራት የተቋቋመ እንደሆነ ዋና ፀሐፊው በውይይቱ ላይ አስታውቀዋል።
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ኢትዮጵያ ለቴክኖሎጂ ዘርፉ ትኩረት ሰጥታ እየሠራች እንደሆነ በመጠቆም በተመድ ፕሮግራም ላይ በንቃት እንደምትሳተፍ መግለፃቸውን ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የተገኘው መረጃ ያሳያል።
@sputnik_ethiopia