ቻይና እና ሩሲያ በሁለተኛው የዓለም ጦርነት የተከፈለውን መስዋዕትነት ከታሪካዊ መዛነፍ መጠበቅ አለባቸው ሲሉ ዋንግ ዪ ተናገሩ
15:57 01.04.2025 (የተሻሻለ: 16:14 01.04.2025)
© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱቻይና እና ሩሲያ በሁለተኛው የዓለም ጦርነት የተከፈለውን መስዋዕትነት ከታሪካዊ መዛነፍ መጠበቅ አለባቸው ሲሉ ዋንግ ዪ ተናገሩ

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ቻይና እና ሩሲያ በሁለተኛው የዓለም ጦርነት የተከፈለውን መስዋዕትነት ከታሪካዊ መዛነፍ መጠበቅ አለባቸው ሲሉ ዋንግ ዪ ተናገሩ
ሁለቱ ሀገራት ታሪካዊ እውነታዎችን ለመቀየር የሚደረጉ ጥረቶችን መከላከል አለባቸው ብለዋል፡፡
ዋንግ ዪ ከስፑትኒክ ጋር በነበራቸው ቆይታ፤ ፋሺዝምን በመዋጋት ረገድ ቁልፍ አጋር እንደመሆናችን መጠን "ከሰላም ወዳድ የዓለም ሕዝቦች ጋር በመሆን ከዓለም አቀፍ ፍትህ ጎን በፅናት መቆም አለብን" በማለት በጦርነቱ ወቅት የተከፈሉ መስዋዕትነቶችን ለማዛባት የሚደረጉ ጥረቶችን አውግዘዋል።
ውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ የቻይና ሕዝብ በጃፓን ወራሪዎች ላይ የተቀናጀውን ድል፣ ሩሲያ በታላቁ የአርበኝነት ጦርነት ያገኘችውን ስኬት እና ዓለም አቀፉን የፀረ-ፋሺስት ጦርነት ታሪክ ለመጠበቅ ዓለም አቀፋዊ ትብብር እንዲደረግ ጥሪ አቅርበዋል፡፡
@sputnik_ethiopia