ቻይና በኢትዮጵያ አየር መንገድ የአውሮፕላን ማረፊያ ፕሮጀክት ላይ ለመሳተፍ ፍላጎት እንዳላት ገለፀች
15:16 01.04.2025 (የተሻሻለ: 15:34 01.04.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
ቻይና በኢትዮጵያ አየር መንገድ የአውሮፕላን ማረፊያ ፕሮጀክት ላይ ለመሳተፍ ፍላጎት እንዳላት ገለፀች
ቻይና ይሄን ፍላጎቷን የገለፀችው የቻይና-አፍሪካ ልማት ፈንድ ምክትል ፕሬዝዳንት ዩ ዡሮይ በቻይና የኢትዮጵያ አምባሳደር ተፈራ ጋር ውይይት ባካሄዱበት ወቅት ነው።
በውይይቱ አምባሳደሩ የሀገራቱን ትብብር ማጠናከርና ኢንቨስትመንትን ማሳደግ እንደሚገባ መግለጻቸውን በቻይና የኢትዮጵያ ኤምባሲ አአስታውቋል፡፡
በኢትዮጵያ የሚገነባውን አዲስ ዓለም አቀፍ የአውሮፕላን ማረፊያ ጨምሮ የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስና ኢትዮ-ቴሌኮምን በተመለከተ ገለጻ አድርገዋል።
ዩ ዡሮይ በበኩላቸው ውይይቱ የሀገራቱን የልማት ትብብር ለማሳደግና አዳዲስ የትብብር መስኮችን ለመፍጠር እንደሚያስችል አስረድተዋል፡፡ የቻይና ልማት ፈንድ በኢትዮጵያ አዲስ በሚገነባው የአውሮፕላን ማረፊያ ፕሮጀክት ላይ የመሳተፍ ፍላጎት እንዳለውም ጠቁመዋል፡፡
@sputnik_ethiopia