ዋንግ ዪ የአሜሪካና ሩሲያ መቀራረብ ለዓለም መረጋጋት ጠቃሚ ነው አሉ
12:15 01.04.2025 (የተሻሻለ: 12:34 01.04.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ዋንግ ዪ የአሜሪካና ሩሲያ መቀራረብ ለዓለም መረጋጋት ጠቃሚ ነው አሉ
የቻይና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዋንግ ዪ አሜሪካና ሩሲያ በቅርቡ ግኑኝነታቸውን ለማስተካከል እያደረጉት ያለው ሙከራ ስጋት የሰፈነበትን ዓለም የሚያረጋጋ ነው ብለዋል።
ከስፑትኒክ ጋር ባደረጉት ልዩ ቃለ ምልልስ "ኃያላን ሀገራት በአስቸጋሪ ጊዜያት የመረጋጋት ምንጭ መሆን አለባቸው" ያሉት ዋንግ ዪ፤ አሜሪካ እና ሩሲያ በተባበሩት መንግሥታት የፀጥታው ምክር ቤት አባላት እንደመሆናቸው መጠን የጋራ ኃላፊነታቸውም ነው ብለዋል፡፡
የሞስኮ-ዋሽንግተን ግንኙነት መጠናከር በዓለም ስትራቴጂካዊ መረጋጋት ላይ መሻሻል ሊያመጣ እንድሚችልም ተስፋቸውን ገልፀዋል፡፡
@sputnik_ethiopia