የሩሲያ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ዩሪ ትሩትኔቭ በናሚቢያ ጉብኝት እያደረጉ ነው
11:27 01.04.2025 (የተሻሻለ: 11:44 01.04.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
የሩሲያ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ዩሪ ትሩትኔቭ በናሚቢያ ጉብኝት እያደረጉ ነው
ትሩትኔቭ በይፋዊ የሥራ ጉብኝታቸው ከናሚቢያ ባለስልጣናት፤ በተለይም ከዓለም አቀፍ ግንኙነት እና ንግድ ሚኒስትር ሰልማ አሺፓላ-ሙሳቪ ጋር በሩሲያ እና ናሚቢያ የኢኮኖሚ ትብብር ዙሪያ ይወያያሉ ተብሎ ይጠበቃል።
ትሩትኔቭ ዊንድሆክ ሲደርሱ የቀድሞ የሀገሪቱ መሪዎች ሳም ኑጆማ እና ሃጌ ጌይንጎብ መቃብር ላይ ጉንጉን አበባ አኑረዋል።
ትሩትኔቭ ከሁለት አስርት ዓመታት በፊት የናሚቢያ የመጀመሪያ ፕሬዝዳንት እና የነጻነት ንቅናቄ መሪ የሆኑትን ኑጆማን እንዳገኙ አስታውሰዋል። የሩሲያው ባለስልጣን ኑጆማ ሶቪየት ህብረት ለናሚቢያ ላደረገችው እርዳታ ምሥጋና ያቀርቡ እንደነበር በመጥቀስ፤ በኑጆማ የቀብር ሥነ-ሥርዓት ላይ መገኘት እንዳልቻሉ እና ጉብኝቱ አክብሮታቸውን ለመግለፅ እድል እንደሰጣቸው ገልፀዋል።
@sputnik_ethiopia