ቴህራን ከዋሽንግተን ጋር በኢራን የኒውክሌር መርሃ ግብር ዙርያ በቀጥታ ለመደራደር ፈቃደኛ አይደለሁም አለች

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱቴህራን ከዋሽንግተን ጋር በኢራን የኒውክሌር መርሃ ግብር ዙርያ በቀጥታ ለመደራደር ፈቃደኛ አይደለሁም አለች
ቴህራን ከዋሽንግተን ጋር በኢራን የኒውክሌር መርሃ ግብር ዙርያ በቀጥታ ለመደራደር ፈቃደኛ አይደለሁም አለች - Sputnik አፍሪካ, 1920, 31.03.2025
ሰብስክራይብ

ቴህራን ከዋሽንግተን ጋር በኢራን የኒውክሌር መርሃ ግብር ዙርያ በቀጥታ ለመደራደር ፈቃደኛ አይደለሁም አለች

የኢራን ፕሬዝዳንት መሱድ ፔዚሽኪያን ለአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በጻፉት ደብዳቤ ቴህራን በሶስተኛ ወገን ሽምግልና ብቻ ለመደራደር ዝግጁ መሆኗን ገልጸዋል።

"ኢራን ከንግግር በጭራሽ ርቅ አታውቅም፤ በዚህ ረገድ ዋሽንግተን የገባችውን ግዴታ መጣሷ አደናቃፊ ነበር፡፡ ይህም በእርግጥ መካስ አለበት፤ በአሜሪካ ላይ ያለው እምነትም መመለስ አለበት። እንዲህ ያሉ የአሜሪካ ድርጊቶች የወደፊት ድርድሮችን አካሄድ ይወስናሉ" ማለታቸውን ኢርና የዜና ወኪል ዘግቧል።

የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አባስ አራቺ ቴህራን ለትራምፕ ደብዳቤ በኦማን በኩል በይፋ ምላሽ መስጠቷን ሐሙስ ዕለት አስታውቀዋል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

@sputnik_ethiopia

መተግበሪያ | X ላይ ይከተሉን

አዳዲስ ዜናዎች
0