በሞስኮ የሱዳን ኤምባሲ የካርቱምን ነፃ መውጣት አከበረ

ሰብስክራይብ

በሞስኮ የሱዳን ኤምባሲ የካርቱምን ነፃ መውጣት አከበረ

'የሉዓላዊነት ምልክት' የሆነችውን ካርቱም መልሶ መቆጣጠር ለሀገሪቱ በጣም ወሳኝ ነው ሲሉ በሩሲያ የሱዳን አምባሳደር ሞሐመድ አል-ጋዛሊ ኤልቲጋኒ ሲራጅ ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል። የካርቱም ነፃ መውጣት ለሰላም አዲስ ምዕራፍ ነው ያሉት አምባሳደሩ፤ ሠራዊቱ እና ሕዝቡ ፈጥኖ ደራሽ ኃይሉን ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ለመደምሰስ ቁርጠኛ ናቸው ሲሉም አክለዋል።

ፈጥኖ ደራሽ ኃይሉ ቅቡል እቅድ እንደሌለው እና ዜጎች ከእነርሱ ጋር ደህንነት እንደማይሰማቸው በመጥቀስ፤ በሱዳን መፃኢ ዘመን ቦታ ስለማይኖራቸው ብቸኛ አማራጫቸው እጅ መስጠት ነው ብለዋል።

"ይህ ከኮርዶፋን እና ዳርፉር በመጀመር፤ ሁሉንም የሱዳን ክልሎች ነፃ ለማውጣት እና እኩል የሀብት እና የስልጣን ክፍፍል ያለበት አዲስ የሰላም ዘመን ለመመስረት የሚደረግ ጦርነት የመጀመሪያ ምዕራፍ ይመስለኛል" ሲሉ በባውማን ሞስኮ ስቴት የቴክኒክ ዩኒቨርሲቲ ፕሮፌሰር የሆኑት አቦበክር መሐመድ አቦበክር ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል።

ይህ ድል ምንም እንኳን ምልክታዊ ቢሆንም የሱዳን ጦር አድካሚውን ጦርነት እንዳሸነፈ ያሳያል ያሉት ፕሮፌሰሩ፤ "ትዕግስት፣ ቁርጠኝነት እና ጠንክሮ መሥራት በመጨረሻ ፍሬ አፍርቷል" ብለዋል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

@sputnik_ethiopia

መተግበሪያ | X ላይ ይከተሉን

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱ
በሞስኮ የሱዳን ኤምባሲ የካርቱምን ነፃ መውጣት አከበረ - Sputnik አፍሪካ
1/5
© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱ
በሞስኮ የሱዳን ኤምባሲ የካርቱምን ነፃ መውጣት አከበረ - Sputnik አፍሪካ
2/5
© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱ
በሞስኮ የሱዳን ኤምባሲ የካርቱምን ነፃ መውጣት አከበረ - Sputnik አፍሪካ
3/5
© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱ
በሞስኮ የሱዳን ኤምባሲ የካርቱምን ነፃ መውጣት አከበረ - Sputnik አፍሪካ
4/5
© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱ
በሞስኮ የሱዳን ኤምባሲ የካርቱምን ነፃ መውጣት አከበረ - Sputnik አፍሪካ
5/5
1/5
2/5
3/5
4/5
5/5
አዳዲስ ዜናዎች
0