የሩሲያ ሙዚየም አፍሪካ ላይ ትኩረቱን ያደረገ ኤግዚቢሽን ሊያዘጋጅ ነው
12:20 30.03.2025 (የተሻሻለ: 12:44 30.03.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
የሩሲያ ሙዚየም አፍሪካ ላይ ትኩረቱን ያደረገ ኤግዚቢሽን ሊያዘጋጅ ነው
የሞስኮው ፑሽኪን ስቴት የሥነ ጥበባት ሙዚየም ዳይሬክተር ኦልጋ ጋላክቲኖቫ አፍሪካ "ፍላጎት እና ሰኬትን መሳቧን የቀጠለች ትልቅ የባህል አድማስ
ነች" ብለዋል።
የአፍሪካ ባህል በሩሲያ ውስጥ ከፍተኛ ቦታ የሚሰጠው ቢሆንም አሁንም ብዙ የማይታወቁ ገጽታዎች እንዳሉት ጋላክቲዮኖቫ ለሩሲያ ሚዲያ ተናግረዋል።
በተለይም ብዙም የማይታወቀው የዘመናዊ አፍሪካ ጥበብ ሊታይ እንደሚገባው አጽንኦት ሰጥተዋል።
የሙዚየሙ ዳይሬክተር አክለውም በዚህ ጉዳይ ዙሪያ የተሠሩ ፕሮጀክቶች እንደሌሉ የገለፁ ሲሆን ሆኖም አሁን ላይ ለውጦች እንዳሉ ጠቁመዋል።
እ.አ.አ በ1912 የተመሠረተው እና ወደ 700 ሺህ የሚጠጉ ሥራዎችን የያዘው የፑሽኪን ሙዚየም በየዓመቱ እስከ 1.3 ሚሊዮን ጎብኚዎችን በመሳብ በሩሲያ በብዛት ከሚጎበኙ ሙዚየሞች አንዱ ነው።
@sputnik_ethiopia