ኢትዮጵያ ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ በቀይ ባሕር ላይ አካታች ትብብርን ቢያበረታታ ተጠቃሚ ይሆናል አለች

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱኢትዮጵያ ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ በቀይ ባሕር ላይ አካታች ትብብርን ቢያበረታታ ተጠቃሚ ይሆናል አለች
ኢትዮጵያ ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ በቀይ ባሕር ላይ አካታች ትብብርን ቢያበረታታ ተጠቃሚ ይሆናል አለች - Sputnik አፍሪካ, 1920, 29.03.2025
ሰብስክራይብ

ኢትዮጵያ ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ በቀይ ባሕር ላይ አካታች ትብብርን ቢያበረታታ ተጠቃሚ ይሆናል አለች

ኢትዮጵያ ከመጋቢት 18 እስከ 19 በብራዚል በተካሄደው በመካከለኛው ምስራቅ እና ሰሜን አፍሪካ የብሪክስ ምክትል ውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች እና ልዩ መልዕክቶች ስብሰባ ላይ ተሳትፋለች፡፡ በብራዚል የኢትዮጵያ አምባሳደር ልዑልሰገድ ታደሰ በስብሰባው ላይ ባደረጉት ንግግር በመካከለኛው ምስራቅ እና ሰሜን አፍሪካ ቀጣና ያሉ ግጭቶች እና ሰብዓዊ ቀውሶች ኢትዮጵያን እንደሚያሳስቧት ገልፀዋል።

ኢትዮጵያ ለሱዳን ግጭት ዲፕሎማሲያዊ መፍትሄ ለማምጣት ጥረት እያደረገች እንደሆነ ያከሉት አምባሳደሩ፤ አቅም ያላቸው የብሪክስ አባል ሀገራት ለሱዳን ሰብዓዊ ቀውስ ድጋፍ እንዲያደርጉ ጥሪ አቅርበዋል።

ኢትዮጵያ በቀይ ባሕር እና በሕንድ ውቅያኖስ ዳርቻ የምትገኝ ከፍተኛ የሕዝብ ቁጥር ያላት ሀገር መሆኗንም አስታውሰው፤ ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ በቀይ ባሕር እና ሕንድ ውቅያኖስ ላይ አካታች ዓለም አቀፋዊ ትብብርን ቢያበረታታ ተጠቃሚ ይሆናል ብለዋል።

ስብሰባው ባወጣው የጋራ መግለጫ በመካከለኛው ምሥራቅ እና በሰሜን አፍሪካ የቀጠሉ ግጭቶች አሳሳቢ እንደሆኑ አበክሮ መግለፁን ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የተገኘው መረጃ ያመላክታል።

@sputnik_ethiopia

መተግበሪያ | X ላይ ይከተሉን

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱ
ኢትዮጵያ ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ በቀይ ባሕር ላይ አካታች ትብብርን ቢያበረታታ ተጠቃሚ ይሆናል አለች - Sputnik አፍሪካ
1/3
© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱ
ኢትዮጵያ ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ በቀይ ባሕር ላይ አካታች ትብብርን ቢያበረታታ ተጠቃሚ ይሆናል አለች - Sputnik አፍሪካ
2/3
© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱ
ኢትዮጵያ ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ በቀይ ባሕር ላይ አካታች ትብብርን ቢያበረታታ ተጠቃሚ ይሆናል አለች - Sputnik አፍሪካ
3/3
1/3
2/3
3/3
አዳዲስ ዜናዎች
0