ኢትዮጵያ ሶስተኛውን የባሕረኞች ማሠልጠኛ አካዳሚ ልትከፍት ነው
17:12 29.03.2025 (የተሻሻለ: 17:44 29.03.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ኢትዮጵያ ሶስተኛውን የባሕረኞች ማሠልጠኛ አካዳሚ ልትከፍት ነው
የኢትዮጵያ ማሪታይም ባለሥልጣን የማሰልጠኛ አካዳሚውን ለመክፈት የሚያስችል የመግባቢያ ስምምነት ከአርባምንጭ ዩኒቨርስቲ ጋር ተፈራርሟል።
አካዳሚው ከባቦጋያ ሎጅስቲክሰ እና ማሪታይም አካዳሚ እንዲሁም ከኢትዮጵያ ማሪታይም ማሰልጠኛ ኢንስቲትዩት ቀጥሎ ለሀገሪቱ ሶስተኛው ማሰልጠኛ እንደሚሆን ተገልጿል።
የኢትዮጵያ ማሪታይም ባለሥልጣን ኢትዮጵያ በ2022 በሎጅስቲክስ አፈፃፀም ከአፍሪካ ቀዳሚ እንድትሆን ለማድረግ እንዲሁም ባሕረኞችን አሠልጥኖ ለዓለም ገበያ በማቅረብ ከመጀመሪያዎቹ አምስት የዓለም ሀገራት ተርታ ለማሰለፍ እየሠራ እንደሚገኝ በማህበራዊ ትሥሥር ገፁ አስታውቋል።
@sputnik_ethiopia