የሩሲያ የገንዘብ ማስተላለፊያ ኩባንያ በኢትዮጵያ የፊንቴክ ዘርፍ ለመሠማራት ፍላጎቱን ገለፀ
12:49 29.03.2025 (የተሻሻለ: 13:14 29.03.2025)
© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱየሩሲያ የገንዘብ ማስተላለፊያ ኩባንያ በኢትዮጵያ የፊንቴክ ዘርፍ ለመሠማራት ፍላጎቱን ገለፀ

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
የሩሲያ የገንዘብ ማስተላለፊያ ኩባንያ በኢትዮጵያ የፊንቴክ ዘርፍ ለመሠማራት ፍላጎቱን ገለፀ
የሩሲያ ዩኒቴለር ኩባንያ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ጉዶቭ ሮማን በሞስኮ የኢትዮጵያ አምባሳደር ገነት ተሾመ ጋር በኢትዮጵያ የኢንቨስትመንት እድሎች ዙሪያ ውይይት አድርገዋል።
ዋና ሥራ አስፈፃሚው ጉዶቭ ሮማን ኩባንያቸው በፊንቴክ እና ቱሪዝም ዘርፍ ያሉ እድሎችን የመዳሰስ ፍላጎት እንዳለው ገልፀዋል።
አምባሳደር ገነት በኢትዮጵያ ቀዳሚ የልማት ግቦች በተለይም በዲጂታል ኢኮኖሚው ዙሪያ ገለፃ ማድረጋቸውን በሩሲያ የኢትዮጵያ ኤምባሲ አስታውቋል።
በተጨማሪም የኢትዮጵያ ኢንፎርሜሽን እና ቴክኖሎጂ ዘርፍ ትልቅ እድሎች እንዳሉት ጠቁመዋል።
አምባሳደር ገነት ኩባንያው ኢትዮጵያን በመጎብኘት ከመንግሥት እና ከግሉ ዘርፍ ጋር ለመተባበር ያሚያስችሉ አማራጮችን እንዲመለከት ጋብዘዋል።
@sputnik_ethiopia