https://amh.sputniknews.africa
ኬኒያ ራሷን እንደ ነጻ ሀገር ላወጀችው ኮሶቮ እውቅና ሰጠች
ኬኒያ ራሷን እንደ ነጻ ሀገር ላወጀችው ኮሶቮ እውቅና ሰጠች
Sputnik አፍሪካ
ኬኒያ ራሷን እንደ ነጻ ሀገር ላወጀችው ኮሶቮ እውቅና ሰጠች“ፕሬዝዳንት ዊልያም ሳሞኢ ሩቶ እና የኬኒያ ሪፐብሊክ ለሀገራችን ነጻ ሀገርነት እውቅና ለመስጠት ለወሰዱት ታሪካዊ ውሳኔ የኮሶቮ ሪፐብሊክ ልባዊ ምስጋናዋን ታቀርባለች። ይህ እውቅና በሀገሮቻችን... 27.03.2025, Sputnik አፍሪካ
2025-03-27T16:40+0300
2025-03-27T16:40+0300
2025-03-27T20:15+0300
sputnik africa
telegram sputnik_ethiopia
https://cdn.amh-img.sputnikglobe.com/img/07e9/03/1b/38926_0:338:832:806_1920x0_80_0_0_db20c2a57e2c1780e92ee304c819fdd7.jpg
ኬኒያ ራሷን እንደ ነጻ ሀገር ላወጀችው ኮሶቮ እውቅና ሰጠች“ፕሬዝዳንት ዊልያም ሳሞኢ ሩቶ እና የኬኒያ ሪፐብሊክ ለሀገራችን ነጻ ሀገርነት እውቅና ለመስጠት ለወሰዱት ታሪካዊ ውሳኔ የኮሶቮ ሪፐብሊክ ልባዊ ምስጋናዋን ታቀርባለች። ይህ እውቅና በሀገሮቻችን መካከል ያለውን ወዳጅነት የሚያጠናክር እና ለተሻሻለ የሁለትዮሽ ትብብርም መንገድ የሚከፍት ነው" ሲሉ የኮሶቮ ፕሬዝዳንት ቪዮሳ ኦስማኔ በኤክስ ገጻቸው ላይ አስታውቀዋል፡፡የሰርቢያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በበኩሉ የኬኒያን ውሳኔ አጥብቆ አውግዟል።ሚኒስቴሩ አክሎም “ይህ እርምጃ በግልፅ የዓለም አቀፍ ሕግን የሚጥስ እና ለሰርቢያ ሪፐብሊክ ሉዓላዊነት እና ግዛታዊ አንድነት ዋስትና የሚሰጠውን የተባበሩት መንግሥታት የፀጥታው ምክር ቤት ውሳኔ 1244 በቀጥታ የሚተላለፍ ነው" ብሏል። ሰርቢያ ለኮሶቮ ነጻ ሀገርነት እወቅና የማትሰጥ ሲሆን ግዛቷንም ኮሶቮ እና ሜቶሂጃ ክልል ብላ ትጠራለች። በኮሶቮ ሰሜናዊ ክፍል የሚኖረው ከፍተኛ የሰርብ ማሕበረሰብ አብዛኛውን ግዜ በሰርቢያ እና በኮሶቮ መካከል የሚፈጠረውን የዲፕሎማሲያዊ ውጥረት ገፈት እንደሚሸከም እና አግላይ ነው የሚለውን የኮሶቮ ፖሊሲ እንደሚቃወም ይነገራል፡፡በእንግሊዘኛ ያንብቡ@sputnik_ethiopia መተግበሪያ | X ላይ ይከተሉን
Sputnik አፍሪካ
feedback.africa@sputniknews.com
+74956456601
MIA "Rossiya Segodnya"
2025
Sputnik አፍሪካ
feedback.africa@sputniknews.com
+74956456601
MIA "Rossiya Segodnya"
ዜናዎች
am_ET
Sputnik አፍሪካ
feedback.africa@sputniknews.com
+74956456601
MIA "Rossiya Segodnya"
https://cdn.amh-img.sputnikglobe.com/img/07e9/03/1b/38926_0:260:832:884_1920x0_80_0_0_c4aeca59e965a523382c66f779241f00.jpgSputnik አፍሪካ
feedback.africa@sputniknews.com
+74956456601
MIA "Rossiya Segodnya"
sputnik africa, telegram sputnik_ethiopia
sputnik africa, telegram sputnik_ethiopia
ኬኒያ ራሷን እንደ ነጻ ሀገር ላወጀችው ኮሶቮ እውቅና ሰጠች
16:40 27.03.2025 (የተሻሻለ: 20:15 27.03.2025) ኬኒያ ራሷን እንደ ነጻ ሀገር ላወጀችው ኮሶቮ እውቅና ሰጠች
“ፕሬዝዳንት ዊልያም ሳሞኢ ሩቶ እና የኬኒያ ሪፐብሊክ ለሀገራችን ነጻ ሀገርነት እውቅና ለመስጠት ለወሰዱት ታሪካዊ ውሳኔ የኮሶቮ ሪፐብሊክ ልባዊ ምስጋናዋን ታቀርባለች። ይህ እውቅና በሀገሮቻችን መካከል ያለውን ወዳጅነት የሚያጠናክር እና ለተሻሻለ የሁለትዮሽ ትብብርም መንገድ የሚከፍት ነው" ሲሉ የኮሶቮ ፕሬዝዳንት ቪዮሳ ኦስማኔ በኤክስ ገጻቸው ላይ አስታውቀዋል፡፡
የሰርቢያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በበኩሉ የኬኒያን ውሳኔ አጥብቆ አውግዟል።
ሚኒስቴሩ አክሎም “ይህ እርምጃ በግልፅ የዓለም አቀፍ ሕግን የሚጥስ እና ለሰርቢያ ሪፐብሊክ ሉዓላዊነት እና ግዛታዊ አንድነት ዋስትና የሚሰጠውን የተባበሩት መንግሥታት የፀጥታው ምክር ቤት ውሳኔ 1244 በቀጥታ የሚተላለፍ ነው" ብሏል።
ሰርቢያ ለኮሶቮ ነጻ ሀገርነት እወቅና የማትሰጥ ሲሆን ግዛቷንም ኮሶቮ እና ሜቶሂጃ ክልል ብላ ትጠራለች። በኮሶቮ ሰሜናዊ ክፍል የሚኖረው ከፍተኛ የሰርብ ማሕበረሰብ አብዛኛውን ግዜ በሰርቢያ እና በኮሶቮ መካከል የሚፈጠረውን የዲፕሎማሲያዊ ውጥረት ገፈት እንደሚሸከም እና አግላይ ነው የሚለውን የኮሶቮ ፖሊሲ እንደሚቃወም ይነገራል፡፡
በእንግሊዘኛ ያንብቡ
@sputnik_ethiopia
መተግበሪያ | X ላይ ይከተሉን