የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ለጅቡቲ የመጠጥ ውኃ ፕሮጀክት የኤሌክትሪክ መሠረተ ልማት ዝርጋታ እንዳጠናቀቀ ገለጸ
10:56 27.03.2025 (የተሻሻለ: 11:14 27.03.2025)
© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱየኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ለጅቡቲ የመጠጥ ውኃ ፕሮጀክት የኤሌክትሪክ መሠረተ ልማት ዝርጋታ እንዳጠናቀቀ ገለጸ

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ለጅቡቲ የመጠጥ ውኃ ፕሮጀክት የኤሌክትሪክ መሠረተ ልማት ዝርጋታ እንዳጠናቀቀ ገለጸ
በሁለተኛ ምዕራፍ የመጠጥ ውኃ ፕሮጀክት 46 ኪ.ሜ መስመር ዝርጋታ እንዲሁም 28 ትራንስፎርመሮች የማስቀመጥ ሥራ እንደተከናወነ አገልግሎቱ አስታውቋል፡፡ በመጀመሪያው ምዕራፍ 8 ሜጋዋት ኃይል፣ 36 ኪ.ሜ የመስመር ዝርጋታ እንዲሁም 8 ባለ 1250 ኬቪኤ ትራንስፎርመር ተከላ መከናወኑን ተቋሙ ገልጿል፡፡
በሁለቱም ምዕራፍ በተከናወነው የመስመር ዝርጋታ በአጠቃላይ 82 ኪ.ሜ መስመር እንደተዘረጋ እና 36 ትራንስፎርመሮች እንደተቀመጡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት አስታውቋል፡፡
የፕሮጀክቱ ሁለተኛ ምዕራፍ ሥራ ተጠናቆ ርክክብ እየተደረገ እንደሆነ አገልግሎቱ ጨምሮ ገልጿል።
@sputnik_ethiopia