የኢትዮጵያ የባሕር በር ጥያቄ ሰጥቶ በመቀበል መርህ ላይ የተመሠረተ ነው ሲሉ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ተናገሩ
18:20 26.03.2025 (የተሻሻለ: 18:44 26.03.2025)
© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱየኢትዮጵያ የባሕር በር ጥያቄ ሰጥቶ በመቀበል መርህ ላይ የተመሠረተ ነው ሲሉ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ተናገሩ

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
የኢትዮጵያ የባሕር በር ጥያቄ ሰጥቶ በመቀበል መርህ ላይ የተመሠረተ ነው ሲሉ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ተናገሩ
የኢትዮጵያ የባሕር በር ጥያቄ አንገብጋቢ እንደሆነ እና ሀገሪቱ ዘላቂ እና የተረጋገጠ የባሕር አማራጭ እንደምትሻ ቃል አቀባዩ ነብያት ጌታቸው አፅንኦት ሰጥተው ተናግረዋል፡፡ ይህ የባሕር በር ጥያቄ በሀገሪቱ የዲፕሎማሲ ተግባራት እየተንጸባረቀ እንደሆነም ቃል አቀባዩ ጠቁመዋል፡፡
“ሀገሪቱ ዘላቂ እና የተረጋገጠ የባሕር ወደብ ስለሚያስፈልጋት የባሕር በር ጥያቄ ወይም የባሕር መተንፈሻ ከቅርብ ግዜ ወዲህ ለኢትዮጵያ አንገብጋቢ ጉዳይ ሆኗል፡፡ ይህ ጉዳይ በዲፕሎማሲ እንቀስቃሴዎቻችን ላይ እየተንጸባረቀ ነው” ሲሉ ለሀገር ውስጥ ሚዲያ ተናግረዋል፡፡
ኢትዮጵያ ዘላቂ የባሕር በር ለማግኘት ጥረቷን አጠናክራ እንደምትቀጥልም ነው ቃል አቀባዩ ያስታወቁት፡፡
“ኢትዮጵያ የተረጋገጠ እና ዘላቂ የባሕር በር ማግኘት የምትፈልገው በሰጥቶ መቀበል መርህ መሠረት በሰላማዊ የዲፕሎማሲ ጥረቶች ነው፡፡ ሀገሪቱ ዘላቂ የባሕር በር የማግኘት ግቧን እውን ለማድረግ ቁርጠኛ ናት” ሲሉም አክለዋል፡፡
@sputnik_ethiopia