የኢትዮጵያ የባሕር በር ጥያቄ ሰጥቶ በመቀበል መርህ ላይ የተመሠረተ ነው ሲሉ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ተናገሩ

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱየኢትዮጵያ የባሕር በር ጥያቄ ሰጥቶ በመቀበል መርህ ላይ የተመሠረተ ነው ሲሉ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ተናገሩ
የኢትዮጵያ የባሕር በር ጥያቄ ሰጥቶ በመቀበል መርህ ላይ የተመሠረተ ነው ሲሉ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ተናገሩ - Sputnik አፍሪካ, 1920, 26.03.2025
ሰብስክራይብ

የኢትዮጵያ የባሕር በር ጥያቄ ሰጥቶ በመቀበል መርህ ላይ የተመሠረተ ነው ሲሉ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ተናገሩ

የኢትዮጵያ የባሕር በር ጥያቄ አንገብጋቢ እንደሆነ እና ሀገሪቱ ዘላቂ እና የተረጋገጠ የባሕር አማራጭ እንደምትሻ ቃል አቀባዩ ነብያት ጌታቸው አፅንኦት ሰጥተው ተናግረዋል፡፡ ይህ የባሕር በር ጥያቄ በሀገሪቱ የዲፕሎማሲ ተግባራት እየተንጸባረቀ እንደሆነም ቃል አቀባዩ ጠቁመዋል፡፡

“ሀገሪቱ ዘላቂ እና የተረጋገጠ የባሕር ወደብ ስለሚያስፈልጋት የባሕር በር ጥያቄ ወይም የባሕር መተንፈሻ ከቅርብ ግዜ ወዲህ ለኢትዮጵያ አንገብጋቢ ጉዳይ ሆኗል፡፡ ይህ ጉዳይ በዲፕሎማሲ እንቀስቃሴዎቻችን ላይ እየተንጸባረቀ ነው” ሲሉ ለሀገር ውስጥ ሚዲያ ተናግረዋል፡፡

ኢትዮጵያ ዘላቂ የባሕር በር ለማግኘት ጥረቷን አጠናክራ እንደምትቀጥልም ነው ቃል አቀባዩ ያስታወቁት፡፡

“ኢትዮጵያ የተረጋገጠ እና ዘላቂ የባሕር በር ማግኘት የምትፈልገው በሰጥቶ መቀበል መርህ መሠረት በሰላማዊ የዲፕሎማሲ ጥረቶች ነው፡፡ ሀገሪቱ ዘላቂ የባሕር በር የማግኘት ግቧን እውን ለማድረግ ቁርጠኛ ናት” ሲሉም አክለዋል፡፡

@sputnik_ethiopia

መተግበሪያ | X ላይ ይከተሉን

አዳዲስ ዜናዎች
0