ኢትዮጵያ በአፍሪካ ሕብረት የሰላም እና ደህንነት ምክር ቤት አቀባበል ተደረገላት
13:28 26.03.2025 (የተሻሻለ: 13:44 26.03.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ኢትዮጵያ በአፍሪካ ሕብረት የሰላም እና ደህንነት ምክር ቤት አቀባበል ተደረገላት
ኢትዮጵያን ጨምሮ የአፍሪካ ሕብረት የሰላም እና ደህንነት ምክር ቤት አዲስ አባል ሀገራት በታንዛንያ አሩሻ ከተማ በተካሄደ ሥነ-ሥርዓት አቀባበል ተደርጎላቸዋል።
በሥነ-ሥርዓቱ አዲሶቹ አባላት ኢትዮጵያ እና ኢስዋቲኒ ምክር ቤቱን በይፋ ተቀላቅለዋል።
ካሜሮን እና ናይጄሪያ በድጋሚ የተመረጡ የምክር ቤቱ አባላት ናቸው።
ኢትዮጵያ ከሚያዝያ ወር አንስቶ በምክር ቤቱ በይፋ በአባልነት ማገልገል እንደምትጀምር ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
@sputnik_ethiopia